martedì

የርክክብ ሥርዓት ሲደረግ

ማዕከላዊው ኮሚቴ ከአዲሱ ሥራ አስኪያጅ ጋር በሚደረገው የርክክብ ሥነሥርዓት ሲፈፀም ውጣ ውረዱ እንዳይበዛ እንዳይከብድ መሆን አለበት፡፡ የርክክርቡ ሥርዓት እየተጓተተ ከመጣ የስራ ድልድሉ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲካሄድ ማድረግ አይቻልም። ... ... ...
ሊኖሩ ከሚችሉት ዋና ዋና ዶኩሜንቶች፣ ንብረቶች፣ መዝገብና ሰነዶች
* የቨርባሌ መያዣ ደብተር (ያለፉትን የማህበሩ እንቅስቃሴዎች ሪፖርት የሚያሳየው መዝገብ)
* የአባላትን ስም ዝርዝር የሚያሳይ መዝገብ
* የተመዘገቡበትን ቀንና ዓመተ ምሕረት እንዲሁም መዋጮዎቻቸው ይሚያሳይ ሰነድ
* ጊዜያቸው ያልወደቀና ሊያገለግሉ ይሚችሉ ማንኛውም ዶሴዎች (የግለሰቦችና የድርጅቶች አድራሻ፣ ስልክ ቁጥር፣ ደብዳቤዎች፣ ወዘተ ...)
* የማህበሩ Statuto (ኦሪጂናል ሰነድ)
* Carta intestata- Partita Ivaየማህበሩ የፖስታ ሳጥን ቁጥርና ቁልፍንብረት
* ቁሳቁስ (በስጦታ የተገኙ እቃዎች፣ ተንቀሳቃሽም ሆነ የማይንቀሳቀሱ ንብረቶች ... )
* የገንዘብ ዶኩመንትስ (የሂሳብ ደብተር፣ ተንቀሳቃሽ ገንዘብ፣ የባንክ ካርድና፣ የestratto conto ወረቀቶች
* የአለፉትን ጊዜያት የባንክ ገንዘብ ገቢና ወጪ የሚያሳይ የባንክ ወረቀቶች ... )
* ጊዜያዊ የሂሳብ አጣሪ ኮሚቴም ተመሥርቶ ክትትል እንዲያደርግበት
* በአለፉት ዓመታት በተቆጣጣሪ ኮሚቴ የኦዲት ክትትል የተደረገባቸውና የሚያሳዩ ሰነዶች ከኖሩ
* የገንዘቡም ሆነ የዶኩሜንቶች ርክክብ የሥራ አስኪያጅ አባሎችና የሂሳብ አጣሪ ኮሚቴ አባላት በተገኙበት እንዲፈፀም ...
* የባንክ ካርዱንና ተንቀሳቃሽ የሆነውን ገንዘብ ለአዲሱ ገንዘብ ያዥ ማስረከብ ...
.
አዲሱ የሥራ አስኪያጅ ክኮሚተው የተወሰኑ ዶኩሜንቶች ከተረከበ በኋላ ሥራውን የሚጀምረው እንደተለመደው አባሎች በሚያቀርቡት ቃለጉባኤ (አጀንዳ) በመያዝ አስፈላጊው ስብሰባ በማድረግና ውሳኔዎችን በማስተላለፍ ይሆናል፡፡
*
የማሕበሩን ገንዘብ አያያዝና በሚመለከት
ቀደም ብሎ በተደረገው ያለኮሚቴ ውሳኔ ምንም አይነት የሂሳብ እንቅስቃሴ እንዳይደረግ ስለተደረገና ባንክ ያለውም ገንዘብ እንዳይወጣ ስለተወሰነ ይህ ሁኔታ በዚሁ መቀጠል አለበት፡፡ የኢትዮጵያውያን ማህበር የሥራ አስኪያጅ ኮሚቴ በአለፉት ሶስት ዓመታት ምንም አይነት ወጪና ገቢ የተደረገ ባለመኖሩ የሂሳብ ሰነድና የስራ ዘገባዎችን አቅርቦ ግምገማ ያደረገባቸው ጊዜያት የሉም። አስፈላጊ ስላልሆነ ነው፡፡ አዲሱ የስራ አስኪያጅ ኮሚቴ ባለው የሂሳብ ደብተር ግልጽ የሆነ የሂሳብ አያያዝ ሥርዓት መመሥረት አለበት። ማንኛውም ወጪና ገቢ ይመዘገባል:: የፈለገው ቢሆን በግለሰብ ደረጃ በእጅ ገንዘብ አይቀበልም:: ማንኛውም ገቢ በማህበር ሂሳብ ገቢ ይሆናል:: መንግስታዊ እውቅና ስለአለው በአልቦ የተመዘገበ በመሆኑ የመንግስት የሂሳብ ተቆጣጣሪ ድንገት መመርመር ቢፈልግ እንኳን ምንጊዜም ዝግጁ መሆን አለበት:: ማንኛውም የገንዘብ ወጪ ከመደረጉ በፊት በማዕከላዊ የሥራ አስኪያጅ በማጆሪቲ የተወሰነበት ቢሆንና ከተወሰነ በኋላም ማህተምና ፊርማ የተደረገበት መሆን አለበት፡፡ ይህም ማለት በግለሰብ ውሳኔና ፈቃድ ምንም አይነት ገንዘብ ወጪ እንደማይደረግ ... ያለኮሚቴ ውሳኔና ያለ ስምምነት ከባንክ ገንዘብ ማውጣት አግባብ ካለመሆኑ ሌላ በሕግ ሊያስቀጣ ይችላል፡፡ ሂሳብ ነክ ነገሮችንና ጠቃሚ የሆኑ መረጃዎችን በየጊዜው ላባላቱ በማቅረብ ማሳወቅ ... ይቀጥላል ...
etiopiainitalia.com

Nessun commento: