lunedì

ለፈገግታ (ክፍል 2)

በኢሜልና በኮሜንት ከደረሱን ውስጥ



ክዚህ በታች ያለው ፅሁፍ በየጊዜው በኢሜል እና በኮሜንት የደረሱንን አሰባስበን እና መርጠን ያወጣናቸው ቀልዶች ናቸው። ለገፁ ቅንብብር እንዲያመቸን በማለት በፅሁፋችሁ ላይ የነበሩትን ተጨማሪ መልዕክቶችና ሰላምታችሁን ከውስጡ በመለያየት ቀልዶቹን ብቻ እንዲወጡ አድርገናል። ለወደፊትም አስፈላጊውን ብቻ ከጽሁፉ ውስጥ በመምረጥ ከስማችሁ ጋር እንዲወጣ ይሆናል።





አገር ቤት ውስጥ የፈረንችና የሀበሻ ዶሮ ይጣላሉ። ጥላቸው የተጀመረው ከፈረንጇ ዶሮ ነው። የፈረንጇ ዶሮ የእኔ እንቁላል ትልቅ ስለሆነ በ 50ሳ ይሸጣል ያንቺ ግን ትንሽ ስለሆነ በ 40ሣ ይሸጣል እያሉ ሲከራረሩ ሀበሻዋ ዶሮ ትናደድና
"እኔ ለ 10ሣንቲም ብዬ ቂጤን አላሰፋም?" አለች ይባላል
ዮናስ (ቦሎኛ)


አንዱ አበሻ ልጅ ዋና ለመማር piscina ይሄድና ሲዋኝ ይሰምጥና መውጣት ያቅተዋል። ከዚያ እዚያው ውሀ ውስጥ እየተንፈራገጠ በአጠገቡ ሰው እንዳለ ሲመለከት አንድ ጠና ያሉ ሰውዬ በpiscinaው አጠገብ ሲያልፉ ያያል። የሰጠመውም ልጅ "አባባ aiutare! ... Io morire! ... እያለ ሲጮህ ሰውዬው ደግሞ ዞር አሉና እንዲህ አሉት " ጣሊያንኛ ከመማርህ በፊት ዋና አትማርም ነበር?" አሉት።
Endale T/Mariam (Roma)


3 ሆነው ባጠፉት ከባድ ወንጀል መሰረት ሶስቱም የሞት ፍርድ ይፈረድባቸዋል አሉ:: እናም በምን መንገድ እንደሚሞቱ የመምረጥ እድሉ ይሰጣቸዋል:: በመርዝ፣ በጋዝ ታፍኖ፣ በስቅላት፣ በጥይት፣ በኤድስ ቫይረስ መወጋት፣
1ኛው "በስቅላት" አለ።
2ኛው "በጥይት" አለ።
3ኛው "በኤድስ ቫይረስ መወጋት" አለ።
ታዲያ ፍርዱ አልቆ ከተከናወነ በኋላ ይሄው 3ኛው ቫይረሱ የተወጋበትን ቂጡን እያሻሸ ምን አለ መሰላቹ ...
"ሸወድኩዋቸው እኮ!" አለ።
እንዴት? ሲሉት ጊዜ
"ኮንደም አድርጌያለሁ"
አብራሃም (ቦሎኛ)


በሽተኛው ዓይን ዶክተር ጋ ይሄዳል:: ዶክተሩ ከመረመረው በሁዋላ ዓይኑ መቀየር እንዳለበት አምኖ ለጊዜው የተገኘው የድመት ዓይን ስለነበረ በዚሁ ይቀይርለታል::
ዶክተር :- "እህ አሁንስ በደንብ ታያለህ ? ንገረኝ ..." ማለት
በሽተኛ :- "በሚገባ ዶክተር:: አያለሁ ብሎ መመለስ"
ዶክተር :- "ምን ይታይሃል?" ሌላ ጥያቄ
በሽተኛ :- "ዓይጥ ነዋ::" ብሎ ዕርፍ
ከቤ


3ት እብዶች ከአማኑኤል ሆስፒታል ሸውደው ለማምለጥ ወስነው መውጫው በር ሲደርሱ በአጋጣሚ ዘበኞቹ የሉም ነበር። በቃ ዘበኞቹ የሉም ማንን እንሸውዳለን? ብለው ወደ ውስጥ ተመለሱ::
Ted 85


ተማሪ :- ባልሰራሁት ስራ ይቀጡኛል ይገርፉኛል?"
ቲቸር :- "እረ እኔቴ እንዴት ሰው ባልሰራው ስራ ይቀጣል? … ይህማ የማይሆን ነገር ነው አልገርፍህም!"
ተማሪ :- "ይምሉልኛል?"
ቲቸር :- "ሙ ት ልጄ! አልመታህም! መድሀኒያለምን! ባልሰራኸው ስራ በፍፁም አትመታም! እንዴ!!!"
ተማሪ :- "እንግዲያውስ ቲቸር አመሰግናለው ዛሬ homework አልሰራሁም"
ከቤ


ሁለት እብዶች ናቸው እየሄዱ ይጨዋወታሉ። አንዱ እብድ አንድ በጣም ትልቅ ተራራ አየና ያንን ተራራ እንግፋው አለው። ለሌላኛው እሱም እሺ ብሎ ላት ላት እስኪላቸው ድረስ ጃኬታቸውን አውልቀው ይገፋሉ። እንደአጋጣሚ አንዱ ሞጭላፋ አይቶቸው በልቡ እየሳቀባቸው ጃኬታቸውን ሞጨለፈው። ትንሽ ቆይተው አንዱ እብድ ዞር ሲል ጃኬታቸው የለም።
"አንተ ጃኬታችንስ?" ቢለው
ያኛው ደሞ ትንሽ የባሰበት ስለነበር "እንዴ አንተ ደሞ በጣም ብዙ እየገፋን በጣም ርቀን ሰለሄድንኮ ነው ማየት ያልቻልነው" አለው ይባላል
ከቤ


ባል ሊሞት ሲያጣጥር ሚስቱን ይጠራና እኔ ስሞት ብዙ ማዘን የለብሽም:: ያለባልም መቅረት የለብሽም:: እንዲያውም ጎረቤታችንን ዘነበን አግቢ:: አደራ ይላታል:: ሚስትም መለስ አድርጋ እንዴት እንዲህ ትለኛለህ? እኔ ፍቅር እንጂ የወንድ ቃር የያዘኝ መስሎሀል? ደግሞ ባገባስ እንዴት ዘነበን አገባለሁ እሱ ስንት ዘመን ሊገልህ የሚፈልግ ጠላትህ አይደል? ብላ ታፈጥበታለች:: ባልም እያቃሰተ ጥላቴማ መሆኑን መች አጣሁት እንደኔው ጥብስ እድርግርሽ እንድትገይልኝ ነበር እንጂ ብሏት እርፍ::
ቅጣው ሀ/ማሪያም (German)


ሁለት እብዶች ተገናኝተው በመንገድ እየተጫወቱ ሲሄዱ አንድ ነገር ተቆልሎ ይመለከታሉ:: እነሱም ሁኔታው ገርሟቸው አጎንብሰው ሲመራመሩ ሁኔታውን ለመረዳት ስላልቻሉ ሁለቱም በጣታቸው ደንቁለው ቀመሱት። ወደ አፍንጫቸው ጠጋ አድርገው ሲያሸቱት አር መሆኑን ሲያውቁ ጊዜ "እፍ እፍ እፍ እፍ እንኳን በእግራችን ያልረገጥነው" አሉ ይባላል።
ዝናሽ


ሁለት ጓደኛማቾች ቁጭ ብለው ጫት እየቃሙ ብው ብለው መርቅነዋል::
አንደኛው በድንገት ብድግ አለና "በዓለም ላይ ያለውን ወርቅ በሙሉ ልገዛው ነው" ሲል
ቀበል አድርጎ "አይ አልሸጥም" አለው::
አብራሃም (ቦሎኛ)

venerdì

ከጣሊያን መንግስት የተሰጠ የነፃ እድል ትምህርት

15/04/2008
ከዶ/ር ዘለቀ እሬሶ
የጣሊያን መንግስት መጪዉን የትምህርት ዘመን ማለትም ከሰፕቴምበር 2008 እስከ ኦክቶበር 2009 ያለዉን የትምህርት አመት አስመልክቶ የዉጭ ሀገር ዜጎችን አወዳድሮ ለአሸናፊዎቹ የነፃ እድል ትምህርት ማለትም እስኮላርሺፕ ለመስጠት አቅዶ በነበረዉ ፕላን መሰረት ሰሞኑን በአገሪቱ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል የነፃ እድል ትምህርት ማስታወቂያ ማዉጣቱ ታዉቆአል::
ለጊዜዉ የነፃ እድል ትምህርቱ ለስንት ተማሪዎች ሊሰጥ እንደታቀደና የእስኮላርሺፑ ትክክለኛ ቁጥር ስንት እንደሆነ በግልፅ የተሰጠ ዝርዝር መግለጫ ባይኖርም እድሉ ሁሉንም የትምህርት ዘርፎች እንደሚያጠቃልል ከወጣዉ ማስታወቂያ መረዳት ተችሏል::
መወዳደር የሚፈልግ ሁሉ በቀጥታ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን ወይንም በየአቅራቢያዉ ያሉትን የጣሊያን አምባሲ ጽ/ቤት በቀጥታ በመጠየቅ አስፈላጊዉን መልስ ማግኘት ይችላል::

ለመወዳደር ምን ያስፈልጋል?
- የትምህርት ደረጃን የሚገልፅ ማስረጃ;
- እድሜዉ ከ 35 አመት በላይ ያልሆነ

የትምህርት ዘርፎች
- የአጭር ጊዜ የጣሊያንኛ ቋንቋ ትምህርት;
- የተለያዩ የዩኒቨርስቲ አጫጭር የሙያ ነክ ኮርሶች;
- የተለያዩ መካከለኛ የሙያ ማሻሻያ ኮርሶች;
- በተለያዩ መስኮች የዲግሪ ትምህርት;
- በተለያዩ መስኮች ከመጀመሪያ ዲግሪ ቀጥሎ ያሉትን ትምህርቶች ማለትም የፖስት ግራጁዌት እስከ ዶክትሬት ድረስ;
- ባህላዊና ሙዚቃዊ አጫጭርና የረጅም ጊዜ ትምህርቶች;
- እና የመሳሰሉትን ያጠቃልላል::
መልካም እድል ለሁላችሁ

giovedì

“ሐሰትና ስንቅ እያደር ይቀላል”

ከዶ/ር ዘለቀ እሬሶ 18.02.08

በአንድ በዴሞክራሲ በበለፀገና ባደገ አገር የፖለቲካ ፓርቲዎች በሚያቀርቡት የወደፊት ፕሮግራም ዝግጅት መሰረት በአገሪቱ በሚደረገዉ የፖለቲካ ምርጫ ለመካፈል ቅስቀሳ የማካሄድና አላማቸዉም ጭምር ምን እንደሆነ በትክክል ለመራጩ ሕዝብ የማሳወቅና የማስረዳት ግዴታ ሲኖርባቸዉ በአንፃሩ መብታቸዉም የተጠበቀ እንደሆነ ይታወቃል:: ይህንንም ስርአትና ደንብ የዴሞክራሲ ጨዋታ (il gioco delle regole della democrazia) በማለት ይጠሩታል::
በዚህ በጣሊያን አገርም እንደ አዉሮፓዉያን አቆጣጠር የፊታችን 13 እና 14 አፕሪል 2008 በሚደረገዉ የፖለቲካ ምርጫ ላይ ለመካፈል የፖለቲካ ፓርቲዎቹ የዉጭ ሀገር ዜጋዉን በተመለከተ የማስፈራራት ዘመቻ፣ ቅስቀሳ፣ ፕሮፖጋንዳና ሽብርም ጭምር በመንዛት ላይ እንደሆኑ በገሃድ ይታያል::
ከዚህ ቀጥሎ የፖለቲካ ፓርቲዎቹን ዝርዝርና ፕሮግራማቸዉን በተለይም በጣሊያን አገር ነዋሪ ለሆኑት አንባቢያን ሊጠቅም ይችላል በማለት ባጭሩ ለማስቀመጥ እሞክራለሁ፣
ስኒስትራ አርኮባሌኖ (Sinistra Arcobaleno):
ባጠቃላይ በተግባር መተርጎም ቢችል የዉጭ አገር ዜጋዉን መብት ሙሉ በሙሉ ሊያስከብር የሚችል ፕሮግራም መስሎ ይታያል;
የዴሞክራትክ ፓርቲ (Partito Democratico):
እምግሬሽንን መቆጣጠር፣ የመኖሪያ ፈቃድ ወረቀት የጊዜ ገደብ ይራዘም፣ መብትና ግዴታን ማሳወቅ፣ የመምረጥና የመመረጥ መብት ማስከበር፣ ጣሊያን አገር ለሚወለዱት ሁሉ የዜግነት መብት ማስከበር፣ ሕገወጥ ወይንም ወንጀለኛ የዉጭ አገር ዜጎችን ማባረር;
እታሊያ ደይ ቫሎሪ (Italia dei Valori):
ወንጀልን ማጥፋት፣ ሕገወጥ ወይንም ወንጀለኛ የዉጭ አገር ዜጎችን ወዲያዉኑ ማባረር; ወንጀለኛ የዉጭ አገር ዜጋ ወደ አገሩ ተልኮ እስር ቤት ይቆያል;
ዩኒዮኔ ዲ ቸንትሮ (Unione di Centro); ወንጀልን ማጥፋት፣ የጣሊያን ዜጎችን ህይወት መንከባከብ፣ ለቁጥጥር ይሆን ዘንድ ለፖሊስ ተገቢዉን መሳሪያ ማቅረብ፣ እምግሬሽንን መቆጣጠር፣ ስራና መኖሪያ ቤት ያለዉ ታክስ በአግባቡ የከፈለ የዉጭ አገር ዜጋ የመኖር መብቱ ይከበራል;
ፖፖሎ ደላ ሊበርታ (Popolo della Libertà)
ወንጀልን ማጥፋት፣ ሕገወጥ ወይንም ወንጀለኛ የዉጭ አገር ዜጎችን ወዲያዉኑ ማባረር; እንተርናሽናል ወንጀልን መቆጣጠር፣ የመኖሪያ ፈቃድ ወረቀት ለሌላቸዉ እንዳይሰጥ፣ ጊዜያዊ እስር ቤቶችን ቁጥር መጨመር፣ ስራና የመኖሪያ ፈቃድ ወረቀት ተለያይተዉ አይታዩም በመሆኑም ስራ የሌለዉ የዉጭ አገር ዜጋ የመኖሪያ ፈቃድ ወረቀቱ አይታደስም;
ላ ዴስትራ (La destra)
በጣሊያን አገር የሚገኝ ማንኛዉም የዉጭ አገር ዜጋ ወደ መጣበት ትዉልድ አገሩ ይመለስ፣ ወንጀልን ማጥፋት፣ ወንጀለኛ የዉጭ አገር ዜጋ ወደ አገሩ ተልኮ እስር ቤት ይቆያል፣ በደንብ መቆጣጠር ይቻል ዘንድ የዉጭ አገር ዜጋ ሁሉ አሻራ የመነሳት ግዴታ አለበት፣ የመኖሪያ ፈቃድ ወረቀት ለሌላቸዉ እንዳይሰጥ፣ የመምረጥና የመመረጥ መብት እንዳይፈቀድ;
ሌጋ ኖርድ (Lega Nord)
ስራና የመኖሪያ ፈቃድ ወረቀት ተለያይተዉ አይታዩም፣ የመኖሪያ ፈቃድ ለማግኘት ገንዘብ ማሳየት ያስፈልጋል ገንዘቡም እንዴት እንደተገኘ ማረጋገጥ ያስፈልጋል፣ በዉጭ አገር ዜጋዉ ላይ ከፍተኛ ቁጥጥር መደረግ ይኖርበታል፣ በመንግስት የመኖሪያ ቤቶች ዉስጥ በሚኖሩት ቤቱ በትክክለኛ ህጋዊ መንገድ እንደተሰጣቸዉ አትብቆ መቆጣጠር፣ ማንኛዉም መንግስታዊ እርዳታ ለዉጭ አገር ዜጋ እንዳይፈቀድ እና የመሳሰሉትን ይጠቅሳል::
እንግዲህ ባጠቃላይ የፓርቲዎቹን ፕሮግራም ስንመለከት ከመጀመሪያዉ በስተቀር ሁሉም የጋራ ቀመራቸዉ የዉጭ አገር ዜጋዉ ሁሉ አደገኛ እንደሆነ በማስመሰል በህብረተሰቡ ላይ ፍርሃትን መዝራት ሆኖአል::
ዉሸትና ስንቅ እያደር ይቀላል እንደተባለዉ ከምርጫዉ በኋላ ሁሉም ይረሳና እንደነበረዉ ይቀጥላል ብቻ ለማየት ያብቃን::

venerdì

በእርሻና ቱሪዝም የስራ መስክ ሰማኒያ ሺህ የዉጭ አገር ዜጎች ጣሊያን እንዲገቡ ተፈቀደ


ሰርገኛ መጣ በርበሬ ቀንጥሱ እንዳይሆን
Decreto flussi 80.000 ingressi stagionali anno 2008
ከዶ/ር ዘለቀ እሬሶ
Bologna, 03 gennaio 2008
በመጀመሪያ ደረጃ እንኳን ለ2008 በሰላም አደረሳችሁ በማለት የያዝነዉ የሥራ አመት የጤና; የሰላም; የደስታና የብልጽግና ይሆን ዘንድ መልካምና ዘላለማዊ ምኞቴን በዚህ አጋጣሚ ለአንባቢያን ለመግለጽ እወዳለሁ::
“ያለማወቅ ከምንም አያድንም” ከሚል ርእስ በመነሳት በተለያዩ ወቅቶች ከዚህ ዌብ ሳይት አዘጋጅ ጋር ባደረግኩት የስራ ትብብር ከተለያዩ አገሮች ከጣሊያንም ሆነ በተለይም ከጣሊያን አገር ዉጪ ከብዙዎቻችሁ ለተላኩልኝ የምስጋና መግለጫና የማበረታቻ መልእክቶች ለያንዳንዳችሁ በግል መመለስ ቢያዳግተኝም ሁላችሁንም ይህንን ጽሑፍ ምክንያት በማድረግ በሰፊዉ አመሰግናለሁ እላለሁ::
ወደ አርእስቴ ልመለስና በእርሻና ቱሪዝም የስራ መስክ ሰማኒያ ሺህ ለሚሆኑ የዉጭ አገር ዜጎች ጊዜያዊ የስራ እድል ይከፍታል ተብሎ የሚጠበቀዉ የጣሊያን መንግስት የኢምግሬሽን ሕግ በዛሬዉ እለት በነጋሪት ጋዜጣ ላይ ታትሞ ይወጣል ተብሎ በጉጉት ይጠበቃል::
የዉጭ አገር ዜጋዉን ሰራተኛ ለመቅጠር ማንኛዉም ቀጣሪ ግለሰብም ሆነ ድርጅት የቅጥር ፎርሙን ቅጽ ከመሙላቱ በፊት የአገር ዉስጥ ምንስቴር በሚቀጥለዉ ወር (ፌብርዋሪ) መጀመሪያ አካባቢ ያወጣል ተብሎ የሚጠበቀዉን መመሪያና ሰፊ መግለጫ መጠበቅ ይኖርበታል::
የሚመጡትም ሰራተኞች ከተለያዩ አገሮች ሲሆን በተለይም ክሰርቢያ; ከሞንተኔግሮ; ከቦዝኒያ; ከማቼዶኒያ; ከክሮዋዝያ; ከሕንድ; ከፓክስታን; ከባንግላደሽ; ከስሪላንካ; ከኡክራይና; ከቱኒዚያ; ከአልባኒያ; ከሞሮኮ; ከሞልዳቪያና ከግብጽ በብዛት ሊመጡ እንደሚችሉ ተጠቅሷል::
ካሁን ቀደም ማለትም ባለፉት አመታት እ.አ.አ. በ2005; በ2006 እና በ2007 ለተመሳሳይ ስራ ጣሊያን አገር እንዲገቡ ተፈቅዶላቸዉ ሰርተዉ ወደያገራቸዉ ተመልሰዉ የነበሩት ሁሉ ለመምጣት ቅድሚያ ሊሰጣቸዉ እንደሚችልም ጭምር በሕጉ ላይ ተጠቅሷል::
በዚህም አመት እንዳለፈዉ ጊዜ የማመልከቻዉ ቅጽ የሚሞላዉ በእንተርኔት መሆኑም ጭምር ተገልጿል::
“ሰርገኛ መጣ በርበሬ ቀንጥሱ” እንዳይሆን ጉዳዩን መከታተል የሚፈልግ ካለ ስር ደርሶ ከመራወጥና ከመንገላተት ይድናል ብዬ በማለት ይህቺን መልእክት አስተላልፋለሁ::
በሚቀጥለዉ እስክንገናኝ መልካም ወቅት
አድራሻ: Dr. Zeleke Eresso
P.O.Box 839
40100 – Bologna
ITALY
Zeleke_eresso@yahoo.it
Tel. 3395764139





giovedì

የጣሊያን ምንስትሮች ምክር ቤት ለ 80.000 ሺህ የዉጭ አገር ዜጎች ጊዜያዊ የስራ ፈቃድ ሕግ አፀደቀ


አ.አ.አ. በ 8/11/2007 የጣሊያን ምንስትሮች ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ ባደረገዉ ስብሰባ ሰማኒያ ሺህ ያህል ለሚሆኑ የዉጭ አገር ዜጎች ጊዜያዊ የስራ ፈቃድ ማግኘት እንዲችሉ አዲስ ሕግ አፀደቀ::
ይህ አዲስ ሕግ ተግባራዊ የሚሆነዉ በነጋሪት ጋዜጣ ላይ ታትሞ ከወጣ በኋላ ስለሆነ ትንሽ ጊዜ መጠበቅ ያስፈልጋል::
የሚመጡትም የዉጭ አገር ዜጎች የስራ ክፍል በእርሻና በቱሪዝም ሲሆን በብዛት የሚመጡትም ከሚከተሉት አገሮች ይሆናል:-
- ሰርቢያ;
- ቦዝኒያ፣
- የቀድሞዉ ይዩጎዝላቪያ ረፑብሊክ ማቸዶኒያ;
- ክሮዋዝያ;
- ህንድ;
- ፓክስታን;
- ባንግላደሽ;
- ስሪላንካ;
- ዩክራይና;
- ቱኒዝያ;
- አልባኒያ;
- ሞሮኮ;
- ሞልዳቪያ;
- ግብፅ ወዘተ ናቸዉ:
በ 2005፣ 2006፣ 2007 የስራ አመት በጊዜያዊ ሰራተኛነት ጣሊያን አገር የመጡ ግለሰቦች ሁሉ ማመልከቻቸዉን ማቅረብ ይችላሉ::
የማመልከቻ ማቅረቢያዉ ሁኔታ ካሁን ቀደም እንደጠቀስኩት በእንተርኔት ይሆናል::

ከዶ/ር ዘለቀ እሬሶ


mercoledì

የጣሊያን የምንስትሮች ምክር ቤት 170.000 የዉጭ ሀገር ስራ ፈላጊዎች ጣሊያን አገር መግባት ይችሉ ዘንድ ሰሞኑን አዲስ ህግ አረቀቀ


ከዶ/ር ዘለቀ እሬሶ
14 11 2007

ካሁን በፊት በተለያዩ አጋጣሚዎች እንደገለፅኩት ሁሉ የጣሊያን መንግስት በየአመቱ ምን ያህል የዉጭ ሀገር ዜጎች ሰራተኞች ለሀገሪቱ ለስራ እንደሚያስፈልጉ በመተመን ጣሊያን እንዲገቡ በየጊዜዉ የአመቱን ህግ ይደነግጋል:: በመሆኑም በዚህ በያዝነዉ የአመት በጀት ፕሮግራም መሰረት በአንቀፅ 2 እንደተመለከተዉ የጣሊያን መንግስት 170.000 ለሚሆኑ የዉጭ ሀገር ዜጎች ማለትም የአዉሮፓ ህብረት አባል አገር ዜጎችን ሳይጨምር በስራ ምክንያት ጣሊያን አገር መግባት የሚያስችል አዲስ ህግ አዉጥቶአል::

የህጉንም ይዘት አጠር ባለ መልኩ ለአንባቢያን ለማስቀመጥ ያህል:-
በመጀመሪያ ደረጃ በህጉ አንቀፅ 2 ላይ እንደተጠቀሰዉ ሁሉ ቁጥራቸዉ 47.100 ያህል ሰራተኞች ከተለያዩ አገሮች ማለትም ክጣሊያን ጋር የቅርብ የጋራ ስምምነት ተፈራርመዉ ከነበሩት ከሚከተሉት አገሮች የሚመጡ እንደሆኑ ተጠቅሷል:-
- ከአልባንያ 4.500;
- ከአልጀሪያ 1.000;
- ከባንግላደሽ 3.000;
- ከግብፅ 8.000;
- ከፍሊፒን 5.000;
- ከጋና 1.000;
- ከሞሮኮ 4.500;
- ከሞልዳቪያ 6.500;
- ከናይጄሪያ 1.500;
- ከፓክስታን 1.000;
- ከሴኔጋል 1.000;
- ከሶማሊያ 100;
- ከስሪላንካ 3.500;
- ከቱኒዚያ 4.000;
- ከተቀሩት አገሮች 2.500::

የስራዉስ ምክንያትና መስክ ምን ምን ይሆናል?
- በቤት ሰራተኛነት 65.000;
- በህንፃ ስራ ሰራተኛነት 14.200;
- በከፍተኛ ትምህርት ተመርቀዉ የሙያ ሃላፊ የሆኑ 1.000;
- በሹፌርነት ልዩ የአዉሮፓ ሰርቲፊኬት ያላቸዉ 500;
- በአሳና ባህር ስራ ላይ 200;
- በተቀሩት የስራ መስኮች 30.000;
- ትምህርትን በስራ በመቀየር 3.000;
- በሙያ ኮርስ ስልጠና 1500;
- በትምህርት 2.500;
- እና በመሳሰሉት::

መቼ ማመልከት ይቻላል?
ይህ ህግ በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ በወጣ በአስራ አምስተኛዉ ቀኑ ማመልከት ይቻላል:: ማመልከቻዉን የሚያቀርበዉ ቀጣሪዉ ግለሰብ ፎርሙን እንተርኔት በመጠቀም መሙላት ይኖርበታል::
zeleke_eresso@yahoo.it
Tel. 3395764139

martedì

“የገበያ ግርግር ለሌባ ያመቻል”


* ዶ/ር ዘለቀ እሬሶ*
... በአገራችን በኢትዮጵያ ገበያ ማለት ምን ማለት እንደሆነ መተንተኑ በዚህ ወቅት አስፈላጊነቱ ጎልቶ ባይታየኝም እንዲያዉ ለማስታወስ ያህል ባጭሩ ገበያ ማለት ምርት አምራቹ ግለሰብ ወይንም ቡድን በተለይም የገጠሩ አርሶ አደር ክፍል ማንኛዉንም ያመረተዉን ጥሬ እቃ ለመሸጥ የሚያቀርብበት አማካይ ስፍራና ለኑሮዉ የሚያስፈልገዉን ለመግዛት የሚሄድበት ማእከላዊ ቦታ ነዉ:: ብቻ ባጠቃላይ እቃና ገንዘብ የመለዋወጫዉ ቦታ ገበያ በመባል ይጠራል:: በመሆኑም የተለያዩ የገበያ ስሞችን እንደነ ጉልት ገበያ፣ መርካቶ፣ እሁድ ገበያ፣ ቅዳሜ ገበያ፣ ሰኞ ገበያ፣ ማክሰኞ ገበያ ወዘተ የመሳሰሉትን መጥቀስ ይቻላል::
... ከላይ እንደጀመርኩት ገበያ የእቃና የገንዘብ መለዋወጫ ቦታ ብቻ ሳይሆን የአገር ሽማግሌዎች የተጣሉ ግለሰቦችን በመጥራት የሚያስታርቁበት ስፍራም ነዉ:: በዚህ የገበያ ቀን ሌባዉንና አታላዩን ለመቆጣጠር ሲባል የጸጥታ አስከባሪዎች በገበያዉ ዉስጥ በመዞር አካባቢዉን ይቃኛሉ:: ይህም ለገበያዉ መልካም ፍጻሜ አመቺ ሁኔታን ይፈጥራል:: ህዝቡም በሰላም የሚፈልገዉን በመግዛትም ሆነ በመሸጥ የፈለገዉን አከናዉኖ ወደየቤቱ ይመለሳል::
... ማህበራዊ ኑሮን በተመለከተ ገበያ ጥቅሙ እጅግ ከፍተኛ ከመሆኑ የተነሳ ህብረተሰቡ ጥላቻን አስወግዶ ተፋቅሮ፣ ተሳስሮ፣ ተቻችሎ፣ ተረዳድቶና ተስማምቶ በአንድነት እንዲኖር በማድረግም ረገድ ከፍተኛ ሚናን ይጫወታል::
ታዲያ በዚህ በምንኖርበት አካባቢ ማለትም “በዉጭዉ አለም” የገበያ ሁኔታ መልኩና ይዘቱ በጣም ለየት ያለ ነዉ:: አንዳንድ እዚህ ነዋሪ የሆኑት የዉጭ ሀገር ዜጎችም የንግዱን አለም ተያይዘዉታል:: ቁጥራቸዉም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመሄድ ላይ ይገኛል:: የንግዱን ይዘትም በሁለት መልኩ ልናገናዝበዉ ይገባል:: በአንድ በኩል የሚያበረታታና እንደ ምሳሌ የሚወሰድ ሲሆን በሌላ መልኩ ደግሞ “የገበያ ግርግር ለሌባ ምቹ ነዉ” የሚለዉን የአያቶቻችንን አባባል የሚያስታዉሰን ይመስለኛል::
... እስቲ የመጀመሪያዉን ለመመልከት እንሞክር:: አንድ በዚህ አካባቢ ነዋሪ የሆነ የዉጭ ሀገር ዜጋ የሚኖርበትን ሀገር ቋንቋ፣ ባህልና የኑሮ ዘዴዉን ጠንቅቆ ከተረዳ ህጋዊ በሆነ መንገድ ሰርቶ ለመንግስት ደግሞ መክፈል የሚኖርበትን የስራ ግብር ከገበረና ከማንኛዉም ወንጀል ነጻ ከሆነ ግዴታዉን በሚገባ ተወጥቶአል ብሎ ማለት ይቻላል:: ይህም ከአንድ ጥሩ ነዉ ከሚባል ዜጋ የሚጠበቅ በጎ ስነምግባር ነዉ:: አብዛኛዉን ጊዜ የዉጭ ሀገር ዜጋ ይህን ግዴታዉን አጥብቆ መወጣት እንዳለበት ተደጋግሞ በተለያዩ የዜና ማሰራጫዎች እንደ ዉዳሴ ማሪያም ሲነገረዉ መብቱን በተመለከተ እንዲከበርለት በሚጠይቅበት ወቅት ግን መልሱ ሰምቶ እንዳልሰማ ይሆንና ግለሰቦችን ወደማይፈልጉት የወንጀል መንገድ ይመራቸዋል:: መብትና ግዴታ ተነጣጥለዉ የሚታዩ ሁለት ነገሮች መሆን የለባቸዉም::
... በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ የግለሰቦች መብት አለመከበር ብዙ የሚያስከትላቸዉ ችግሮች ሊኖሩ እንደሚችሉ መዘንጋት የለብንም:: የጸጥታ ችግር፣ የሌብነት፣ የማጭበርበር፣ የሽርሙጥና፣ የድራግ ሱስ ወዘተ ብቻ በአጠቃላይ “እንደምንም ገንዘብ ብቻ ላፍራ” የሚል መፈክር ተይዞ ይነሳና መጨረሻዉ ዉድቀት ከመሆንም ያልፍና ሰላማዊ ኑሮ ቀርቶ በምትኩ መፈራራትና ጥላቻ የመሳሰሉት ይነግሳሉ:: ብልጠትን፣ ማጭበርበርንና ዉሸትን መሰረት በማድረግ የሚሰራን ስራ እንደ ስራ ሊንቆጥረዉ አይገባም::
... በኢጣሊያን ሃገር ዉስጥ በግምት ወደ ሶስት ሚሊዮን የሚጠጉ የዉጭ ሐገር ዜጎች እንደሚኖሩ ይነገራል:: ይህ ቁጥር ብዙ መስሎ ቢታይም ከሌሎች የአዉሮፓ አገሮች ጋር ሲወዳደር አነስተኛ ነዉ:: በተጨማሪ ለጊዜዉ ቁጥራቸዉ በትክክል የማይታወቅ የመኖሪያ ፈቃድ ወረቀት የሌላቸዉ የድብቅ ስራ በመስራት ኑሮን ለመወጣት የሚታገሉም ጭምር እንዳሉ ነዉ::
... አንዳንድ የዜና ማሰራጫዎች አልፎ አልፎ የዉጭ ሃገር ዜጋን በተመለከተ ትክክለኛ ያልሆነ መልክት ያስተላልፋሉ:: የዉጭ ሃገር ዜጋንና ወንጀልን አጣምረዉ በማቅረብ የዉጭ ሃገር ዜጋዉን ሁሉ ወንጀለኛ አድርገዉ ያቀርባሉ:: በዚሁ የተሳሳተ መልክት የተነሳ በየመንገዱ “አሁንስ እነኚህ የዉጭ ሃገር ዜጎች በዙ ይዉጡልን” የሚሉትንና የመሳሰሉትን ዘረኛ ቃላት መስማቱ ጆሮዬ ዳባ ልበስ ሆኖአል:: ይህም እንግዳዉንና አስተናጋጁን አይጥና ድመት ሆነዉ የጎሪጥ እንዲተያዩ ያደርጋቸዋል::
... ለማጠቃለል ያህል በዚህ ብልጠትና እራስ ወዳድነት በበዛበት በተለይም ባሁኑ ወቅት የዉጭ ሀገር ዜጋዉ ከምን መጠንቀቅ አለበት:
... 1. በማሳወቅና በማስተማር ፋንታ “አንተ አታዉቅም፣ ቋንቋ አትችልም፣ እኔ እሰራልሀለሁ፣ እኔ አስብልሃለሁ” ከሚሉት የአፍ እርዳታ ሰጪዎች በሚገባ መጠንቀቅ;
... 2. በተቻለ መጠን ተደብቆ በጥቁር መስራትን ማስወገድና ለመንግስት አስፈላጊዉን የስራ ግብር በወቅቱ መክፈል;
... 3. በስራ የሚተዳደረዉ የዉጭ ሀገር ዜጋ እድሜ ገፍቶ ጡረታ እንዳለ በመረዳት አስፈላጊዉን የጡረታ ማስከበሪያ የታክስ ሁኔታ ከሚመለከተዉ መንግስታዊ አካል የራስን ሁኔታ መከታተል;
... 4. ትምህርትን በተመለከተ በመማር ላይ ያለዉ ትምህርቱ “ጊዜን ገዳይ ብቻ” እንዳይሆንበት ተጠንቅቆ ትምህርቱ እንዳበቃ ስራ ማግኘት የሚያስችለዉን የትምህርት አይነት መማር እንዳለበት ከሚያዉቁት ሰዎች ጠይቆ መረዳት;
... 5. ከዘረኝነት በሽታ፣ ከሃይማኖት የበላይነት፣ ከአጉል ፉክክር፣ ከማይጠቅም ምቀኝነት፣ ከማያሳድግ ሃሜትና አሉባልታ እና ከመሳሰሉት ኋላ ቀር አመለካከቶች በመራቅ ሰላማዊ ኑሮን ከሚያስፋፉ የህብረት ክፍሎች ጋር መተባበር;
... 6. ግዴታን ከተወጡ የግል መብትንም ለማስከበር መጣር::
በሚቀጥለዉ እስክንገናኝ መልካም ቆይታ


የፋሺስት ኢጣሊያ ግፍ አሁንም ያነጋግራል


19 07 2008
ከዛሬ 73 ዓመት በፊት የፋሺስት ኢጣሊያ ሠራዊት በኢትዮጵያኖች ላይ አሰቃቂ ግፍና ጭፍጨፋ መፈፀሙ የቅርብ ጊዜ ታሪካችን ነው። በወቅቱ የፋሺስት ሠራዊት በተጠቀመው የመርዝ ጋዝ ያደረሰው እልቂት ከፍተኛ ነበር። በዚያን ጊዜ የፋሺስት ሠራዊቱ የጦር አዛዥ ከነበሩት መካከል በጨካኝነቱ ለሚታወቀው ጄነራል አልፒኒ መታሰቢያ የተተከለው ሐውልት እስካሁን ድረስ እየተከበረ መገኘቱ አዲስ ውዝግብን ሊቀሰቅስ ችሏል።
በ1936 እ.ኤ.አ. በአልፒኒ ስም የቆመው ሐውልት በራሱ በአልፒኒ ምስል የተቀረፀ ነው። ይህ በሰሜን ኢጣሊያ የሚገኘው የአልፒኒ መታሰቢያ ሐውልትና በስሙ የሚጠራው መንገድም ”አልፒኒ ኖርዘን ኢታሊያ” የሚባል ነው። በኢትዮጵያውያኖች ላይ ጭፍጨፋን የመራ ግለሰብን እስካሁን ድረስ እንደ ጀግና ተቆጥሮ መከበሩ ብዙዎችን ያስደነቀና ያስደነገጠ ጉዳይ ሊሆን ችሏል። ሰሞኑን ወደ ሰሜን ኢጣሊያ አቅንተው የነበሩት በኢጣሊያን የኢትዮጵያ አምባሳደር ግሩም አባይ በተመለከቱት ነገር እንደተገረሙ ተናግረዋል።
የአልፒኒን ሐውልት ያሠራው የፋሺስት ኢጣሊያ መሪ የነበረው ቤኒቶ ሙሶሎኒ ነበር። አልፒኒ በተለይ በጦርነቱ ወቅት የሚታወቅበት ፋሺስቱ ሠራዊት ዘረፋ እንዲያካሂድ፣ እንዲገድልና አስገድዶ እንዲደፍር ግልፅ ትዕዛዝ በመስጠቱ ነበር። እ.ኤ.አ. በ1936 የተተከለው የአልፒኒ መታሠቢያ ሐውልት፣ በዚያን ጊዜ ቢሆን ተቃዋሚ ያላጣ እና ይኸው ተቃውሞ ለበርካታ ዓመታትም ሳይቋረጥ ቆይቷል። በሐውልቱ ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቃት የተሰነዘረው የሁለተኛው የዓለም ጦርነት ሳይጠናቀቅ በፊት ሲሆን፣ ከዚያም በተከታታይ በ1956፣ በ1959፣ በ1966 እና በ1979 ጥቃት ተሰንዝሮበት በከፊል ሊጎዳ ችሏል። በአሁኑ ወቅት በአልፒኒ ሐውልት ጉዳይ ላይ ተቃወሞውን እያቀረበ የሚገኘው 'sudtiroler schutzenbund' የተባለ የባህል ተቋም ነው። ይኸው ተቋም አምባሣደር ግሩም ዓባይን ወደ ሰሜን ኢጣሊያ “ሳውዝ ትሮይል” ጋብዞ በጉዳዩ ላይ ለመነጋገር ችሏል። ለአምባሳደር ግሩም ዓባይ የጦር ወንጀለኛውን የአልፒኒ ሐውልትን ወስዶም አሳይቷል። በኢጣሊያ በርካታ ከተሞች የተተከሉ የፋሺስት ኢጣሊያ የጦር መሪዎች መታሰቢያ ሐውልቶችና በስማቸው የተሰየሙ መንገዶች ይገኛሉ። ከአልፒኒ ባልተናነሰ የጦር ወንጀል የፈፀሙ ቪያ-አምባ-አላጊ እና ቪያ ፓተር ጂሊያኒ የተባሉ የፋሺስት የጦር መሪዎች ስም በጣሊያን መንገዶች ይጠራሉ። አምባሳደሩ ከባህል ተቋሙ ጋር ሁለት ሰዓት የፈጀ ወይይት ያደረጉ ሲሆን፣ ምንም ምንኳ የኢትዮጵያ ህዝብ ጣልያኖችን ይቅርታ ያደረገላቸው ቢሆንም በሰሜን ኢጣሊያ የጦር ወንጀለኛውን የአልፒኒ ሐውልትን በተመለከተ “ሐውልቱ በኢትዮጵያውያኖች ላይ የተፈፀመውን ጭፍጨፋ በድጋሚ ጎልቶ እንዲታይ የሚያደርግ ነው” ሲሉ ተናግረዋል። የባህል ተቋሙ፣ በኢጣሊያ በጦር ወንጀለኝነት የሚታወቁ የጦር አዛዦች ስም የቆሙ ሐውልቶችና በስማቸው የሚጠሩ መንገዶች ዝርዝር ለኢትዮጵያ መንግሥት እንደሚሰጡ ቃል ገብተዋል። የባህል ተቋሙ አባል የሆኑት ፖል ባቸር እንደተናገሩት፣ ከጣልያን መንግሥት የሚጠበቀው ነገር ጣልያንን ካዋረዳት የፋሺስቶች ተግባር ምን ያህል ርቀት እንዳለው እና በመላው ጣሊያን የሚገኙ የፋሺስት ሠራዊት መታሰቢያዎችን ማስወገድ ነው ብለዋል።
ሞሶሎኒ በኢትዮጵያ ላይ ያወጀው ጦርነት የተጀመረው እ.ኤ.አ. ጥቅምት 3 ቀን 1935 ዓ.ም ነበር። በጊዜው የኢትዮጵያ ንጉሥ ጉዳዩን በሊግ ኦፍ ኔሽን አሰምተው ነበር። የፋሺስት ጦር ኢትዮጵያ ላይ የተጠቀመውን የመርዝ ጋዝ ከጀርመን ናዚ ጋር ለሚያካሂደው ጦርነት መሞከሪያ ለማድረግም ነበር። የፋሺስት ጦር ድርጊትን አስመልክቶ ብሪታኒያዊው ሐኪም ጆን ሜሊይ እንደገለፁት፣ “ይህ ጦርነት አይደለም፤ በጭካኔ ደም ማፍሰስ ብቻም አይደለም፣ ሊባል የሚችለው ነገር፤ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ መከላከያ የሌላቸውን ኢትዮጵያውያን በአሰቃቂ ሁኔታ በመርዝ ጋር መጨረስ ነው” ብለዋል። የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ተወካይ የነበረው ማርሴል ጂኖድ በጊዜውን የዓይን እማኝነቱን የገለፀው “በየቦታው በመሬት ላይ የተጋደሙ ሬሳዎች ነበሩ፣ የሰው እግሮችና ሳምባዎች ሳይቀሩ በመሬት ላይ ይታያሉ። ያየሁት ነገር አሰቃቂ ብቻ ተብሎ የሚታለፍ ብቻ አይደለም” ሲል ተናግሯል። ጦርነቱ በኋላ የፋሺስት አጣሊያ መንግሥት ለፈፀመው የዘር ፍጅት በዓለም አቀፉ የጦር ፍርድ ቤት ለመክሰስ ታስቦ የነበረ ቢሆንም በወቅቱ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ተሸናፊ በመሆኑ ሊቀር ችሏል። የጣሊያን መንግሥት ግን በካሳ መልክ ለኢትዮጵያ የ25 ሚለዮን ዶላር ቢሰጥም አሁንም ድረስ በይፋ ይቅርታ አልጠየቀም።
ኢትዮጲያ ዛሬ


በጣሊያን የሮማው ኦሎምፒክ ጊዜ
(ዘመን የማይሽረው ሕያው ታሪክ)


ሮም የኢትዮጵያ ደመኛ አገር የነበረችዋ የጣሊያን ዋና ከተማ ናት። በሮም፣ ቤኒቶ ሙሶሊኒ ኢትዮጵያን በወረረ ጊዜ፣ በአዲስ አበባ የጣሊያን ባንዲራ በመተከሉና ኢትዮጵያ በጣሊያን እጅ በመውደቋ የድንፋታ ንግግር ለአገሬዉ ሕዝብ ያደረገበት ከተማ ናት። ከሃያ ስድስት አመታት በኋላ፣ እንደ ኢትዮጵያዉያን አቆጣጠር በ 1952 ዓ.ም ባንዲራችን መሬት ወድቆ ጮቤ በተረገጠባት ከተማ የኢትዮጵያ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ባንዲራ ከፍ ብሎ ተዉለበለበ። በዚያን ቀን ታሪክ ተሰራ።


ጥንታዊት ሮማ ዳግም የታደሰች መስላለች። መንገዶቹ ሁሉ የፊት ማያ መስተዋት መስለዋል። እንዴት አደርሽ ጣሊያን? እንዴት አደርሽ ሮማ? የሚል የጣሊያን ሬዲዬ ድምፅ ይስተጋባል። ሁሉም የክቱን፤ እንዲሁም ደግሞ የማእረግ ልብሱን በየበኩሉ ለብሶ የኦሊምፒክ ውድድር የመዝጊያውን ቀን ሥነ-ሥርዓት ለማየትና ለመሰናበት ከየቦታው ወደ ሮማ ስታዲየም ይጐርፋል። ይተማልም።

ጊዜው እ.ኤ.አ. 1960 ነው። ኢትዮጵያ በኦሊምፒክ መድረክ ላይ በብስክሌትና በሩጫ ውድድር የተካፈለች ሲሆን፤ የብስክሌት ተወዳዳሪው በውድድሩ ላይ ተጠልፎ ከወደቀበት ተነስቶ 7ኛ ሊወጣ ቻለ።

ገረመው ደንቦባ።
የመጨረሻውን እና ተናፋቂውን ማራቶን ለመጀመር «በስመ-አብ ወወልድ« ብሎ አማትቦ እስኪጨርስ ድረስ እንኳ ፋታ አላገኘም። የውድድሩን መጀመር የሚያበስረው የሽጉጥ ድምፅ አስደነገጠው። እንደ ሽጉጧ ጥይት ተተኩሰው ያፈተለኩትን ከተለያዩ ክፍለ- ዓለማት ከተውጣጡ 79 ወጣት ተወዳዳሪዎች ጋር ተከትሎ ተነሣ። በሕልሙ ይሁን በእውኑ በውል አልታወቀውም። ግን መሮጡን አላቆመም፤ ይሮጣል፤ ይቀድማል፤ ወደፊት ይገሰግሣል... ይሁን እንጂ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ነበር ውድድሩ ላይ መሆኑን የተገነዘበው። ያውም ማራቶን! 42 ኪሎ ሜትር ከ195 ሜትር ርቀት! ከተወዳዳሪዎቹ መካካል ለየት ያለ ቀለም ያለው አንድ አትሌት ይታያል። ታዲያ ማንም ስለ አንድ አፍሪቃዊ ብቸኛ ጥቁር አትሌት ቦታ መስጠት ቀርቶ በንቀት መልክ ነበር የሚገላምጡትና የሚሣለቁበት። በውድድሩ መንፈስ ውስጥ ብቻ የነበረው ቆፍጣናው አፍሪቃዊ የIትዮጵያ ልጅ ከፊት መሪ ተወዳዳሪዎቹ ጋር ፍልሚያ ተያይዟል።

ውድድሩን በመቀባበል በየኪሎ ሜትሩ ፍጥነታቸውን በመጨመር አያንዳንዱ ተወዳዳሪ ለሐገሩ ክብር የጭንቀት ውድድር ውስጥ ይገኛል። ብርቅዬውና ውዱ የኢትዮጵያ ልጅዓበበ ቢቂላ ከእነዚህ ተወዳዳሪዎች አንዱ ነው። ውድድሩ ከተጀመረ 20 ደቂቃ Aልፎታል። አበበ በመሪነት ካሉት መካካል አንዱ ቢሆንም ከተወዳዳሪዎቹ ጋር አብሮ መጓዝ ግን ፈፅሞ አልተዋጠለትም። ተፎካካሪዎቹ ሣያስቡት የፊት መሪነቱን ቦታ ይዞ ፍጥነቱን በመጨመር ውድድሩን ቀጠለ። ማንም ሯጭ በአጠገቡ የለም። ለዓለም ሕዝብና ለመላው የጣሊያን ነዋሪ የሚተላለፈው የዜና ማሰራጫ ለአንድ አፍታ ፀጥ Aለ። ውድድሩን የሚያስተላልፈው ጣሊያናዊ ጋዜጠኛም አይኑ ፈጧል። ይንቆራጠጣልም። የደነገጠም የተገረመም ይመስላል። ድንገት ከሕልሙ አንደባነነ ሰው ድምፁን ከፍ በማድረግ መጮህ ጀመረ። «ምን ዓይነት ጉድ ነው! እኔ አላምንም! ይገርማችኋል! ማ ማ ሚ ያ! ይደንቃል!» ይል ጀመር። ንግግሩን በመቀጠል «አንድ ጥቁር አፍሪቃዊ በማይታመን ሁናቴ ውድድሩን ብቻውን፤ የመሪነት ቦታውን እስካሁን በሞኖፖል ተቆጣጥሮታል። ጥቁር እፍሪቃዊ ነው።» ደጋግሞም የጥቁርነቱን ምልክት ይናገራል፤ ይጮሃል፤ ይለፈልፋልም። Iትዮጵያዊ መሆኑን ግን በትክክል ያውቃል። አንዳይናገረው አንደበቱን የቆለፈው ታሪክ ግን አለ። Iትዮጵያ ጣሊያን ባዘጋጀው ኦሊምፒክ ማሸነፍ ማለት ጣሊያን ለሦስተኛ ጊዜ በኢትዮጵያ እንደተሸነፈች ነበር ለጋዜጠኛው የታየው። ሣልሣዊ ውርደት!! ጋዜጠኛው አሁንም የሬዲዬ መልእክቱን ማስተላለፉን አላቆመም። «...ማ ማ ሚ ያ! ፍጥነቱን ከልክ በላይ ጨምሯል፤ የድካም ምልክት አይታይበትም፤ ይጨርስ አይጨርስ ግን በትክክል አላውቅም፤ የሚገርማችሁ ነገር ቢኖር አግዜር አንደፈጠረው ባዶ አግሩን ነው፤ ኢትዮጵያዊ ነው። አቢሲኒያዊ ነው። ይጨርሣል ብዬ አልገምትም ...» ብሎ ያሟርታል። ውድድሩን በጥሞና በመከታተል ላይ የነበሩትና የአበበም አሰልጣኝ አንዲሁም የቡድኑ መሪ ሆነው የሄዱት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ውስጣቸው ተረብሿል። አንዴ ይቀመጣሉ፤ ሌላ ጊዜ ይነሣሉ... በተመስጥኦ ውጤቱን ይከታተላሉ። በዚህ መካከል አንድ እንግሊዛዊ ጋዜጠኛ በለሰለሰ አንደበትና ሥነ-ሥርዓት ጐንበስ በማለት «አቶ ይድነቃቸው ባልሣሣት እርስዎ ነዎት?« በማለት ሲጠይቃቸው «አዎ ምን ነበር?» በማለት መለሱለት። ጋዜጠኛውም ቀጠል አድርጐ «የእርስዎ ተወዳዳሪ ውድድሩን በከፍተኛ ርቀት በመምራት ላይ ነው። ውጤቱ ምን ይመስለዎታል?» በማለት ሲጠይቃቸው፤ «ለጥያቄህ አመሰግንሃለሁ። ውጤቱን በኋላ አብረን አናየዋለን።» ነበር ያሉት በትህትና። የውድድሩን ሂደት በጥሞና Eእየተከታተሉ የሚዘግቡት የተለያዩ አገር ጋዜጠኞችም ቢሆኑ ከጣሊያናዊው ጋዜጠኛ ብዙም ባይለዩም በንግግራቸው፤ በአገላለጣቸውና በአቀራረባቸው ሁሉም የአበበን ሥእላዊ ድርሰት በየተራ የሚያነቡ ይመስላሉ። የአቤን እጅ አወዛወዝ፤ የእግር አጣጣሉን፤ ቁመናውን፤ አፍሪቃዊነቱን ጥቁርነቱን በመደጋገም ለመግለፅ ይሞክሩ እንጂ የአበበን ውስጣዊ መንፈስና ሞራለ-ጠንካራነት ብሎም አይበገሬነት ግን ከርሱ በስተቀር ማንም የተረዳው ሰው አልነበረም። ውድድሩን በከፍተኛ ፍጥነትና በሙሉ ኃይል እንዲሁም በአስተማማኝ ርቀት የሚመራው አበበ፤ ሮማ ስታዲዮም ሲደርስ ተመልካቹ ሕዝብ ከመቀመጫው ብድግ በማለት ጭብጨባውን አቀለጠለት። ጀግናው ኢትዮጵያዊ አዲስ የኦሊምፒክ ክብረ ወሰን በባዶ እግሩ በመስበር አሸነፈ። ድልን ተቀዳጀ። ድሉ ለኢትዮጵያ ብቻም ሣይሆን ለአፍሪቃም ጭምር ሆነ። በነገራችን ላይ አበበ ውድድሩን እንደቀላል ነበር የጨረሰው። በውጤቱም ቀደም ሲል በሩሲያዊው ሰርጌይ ፖፖቭ በ2፡30፡00 የተያዘውን የሰዓት ሪኮርድ በ2፡16፡02 አሻሻለው። በዚህ በሮሙ ውድድር የተሰለፈው አበበ ዋቅጅራ ደግሞ እግሩ ፈንድቶ በሰርጌይ ፖፖቭ ለጥቂት ተቀድሞ 7ኛ ወጣ። ከርሱ በኋላ ተከታትለው በመግባት ላይ ያሉትም ተራ በተራ ፍንግል እንደያዛት ጫጩት ሜዳ ላይ ተዘርረዋል። በቃሬዛም በድጋፍም የተወሰዱ ነበሩ። አበበ ግን ለውድድሩ እንደሚዘጋጅ ተወዳዳሪ ጂምናስቲክ ይሠራል። አካሉንም ያዝናናል። አበበ ልዩ ተስጥዎ የነበረው ሞራለ-ጠንካራ አትሌት ነበር። ኢትዮጵያ ከሮማ ኦሊምፒክ በፊት በ1956 በሜልቦርን ኦሊምፒክ ተሣትፋ ነበር። ተወዳዳሪ ሆነው የቀረቡት በ100 ሜትር አቶ ንጉሤ ሮባ፤ እንዲሁም በማራቶን ባሻ ተብለው የሚጠሩት ዛሬ በሕይወት ያሉና የፌዴሬሽኑ ዘበኛ ነበሩ። በውጤቱም ባሻ ውድድሩን ጨርሰዋል። አቶ ንጉሤም አፈሩን ያቅልልላችውና ውድድሩን ፈፅመዋል።

የዓለም የማራቶን ውድድር ስም ከተነሣ ከሮማ ኦሊምፒክ በፊት በተደረጉት ውድድሮች በርካታ ተወዳዳሪዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል። ብዙዎቹ አቋርጠዋል። በዚያን ዘመን ያሸነፉትም ቢሆኑ ከ3 ሰዓት በላይ ነበር የፈጀባቸው። አበበ ግን በማይታመን ሁናቴ ከላይ በተገለጠው መሠረት አዲስ ሬኮርድ ነው ያስመዘገበው።

አበበ ከሮማ ኦሎምፒክ ሜዳ የአበባ ጉንጉንና የማራቶን የወርቅ ሜዳሊያውን በአንገቱ አስገብቶ ወደ እናት ሐገሩ በደስታ ተመለሰ። የሐገሩ ሕዝብም በጭብጨባ፤ በደስታ፤ በእልልታና በጭፈራ ተቀበለው። በተለይም ደግሞ የክፍሉ የሥራ ባልደረቦች የሆኑት የክብር ዘበኛ ጦር አባላት በልዩ ልዩ ዘፈንና ወኔ በተሞላበት፤ በከፍተኛ የሐገር ቅር ስሜት ነበር የተቀበሉት። የዘመሩለትም።
አቤም ለሐገሩ ላስገኘው ክብር፤ ለራሱም ላስመዘገበው ክብረ-ወሰን ለሽልማት ግርማዊነታቸው ፊት ቀረበ። «ደጉ ንጉሣችንም» የምክትል አሥር አለቃነት የበታች ሹማምንቶች ማእረግ አከናነቡት። አቤት ደግነት ይሉታል ይህ ነው!

አበበ ቢቂላ በማራቶን ብቻም ሣይሆን በ5ሺህ፤ በ10ሺህ፤ በ21 ኪሎ ሜትር፤ በ12 ኪሎ ሜትር በሄደበት ሐገር ሁሉ ማሸነፍ ብቻም ሣይሆን ክብረ-ወሰንም ጭምር ነበር የሰበረው። አንድ መረሣት የሌለበት ጉዳይ ቢኖር አበበ በሮም ኦሊምፒክ ውድድር ካሸነፈ በኋላ ለጋዜጠኞች በሰጠው ቃለ-ምልልስ ላይ የተናገረው ነው። ይኸውም፤ «... እኔ የዛሬ ኦሊምፒክ አሸናፊ ከዓለምም አንደኛ ነኝ። በሐገሬ ላይ ግን ሁለተኛ ነኝ» ነበር ያለው። እንዴትና ለምን? ተብሎ ለተጠየቀው ጥያቄ ሲመልስም «እኔን የሚበልጠኝ ጓደኛ አለኝ። ይበልጠኛል። በውድድሩ ላይ ሣይሣተፍ የቀረውም በሰውነቱ ላይ ዘጠኝ ቦታ ቡግንጅ ወጥቶበት ነው። ስሙም ዋሚ ቢራቱ ይባላል። ስለዚህ ነው ብቻዬን የመጣሁት» ብሏል። የኢትዮጵያ ስፖርት ጋዜጠኞች ስለ ዋሚ ቢራቱ ያላሉት የለም። ሞራለ-ጠንካራውና «እድለ ቢሱ» ዋሚ ለኦሊምፒክ አይመረጥ እንጂ ከአበበና ከማሞ ወልዴ ጋር ብዙ ዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይ ተካፍሎ አሸንፏል። ከማሞና ከአበበ ጋርም ተከታትሎ ገብቷል። ዛሬ ዋሚ ቢራቱ በሕይወት የሚገኙ አዛውንትና የ5 ልጆች አባት ናቸው። እኚህ እውቅ አትሌት የሐገሪቱ ባለውለታ፤ በውድድር ዘመናቸው ፉክክር ሁሉ ለሐገሩ ክብር ማስገኘት ብቻ ስለነበር ምንም ዓይነት ቋሚ ንበረትና ሃብት አልነበራቸውም። ምሥጋና ይግባቸውና ዛሬ አቶ አላ-ሙዲ የተባሉ ባለቱጃር መኖሪያ ቤት አሠርተውላቸዋል። የአበበ፤ የማሞና የዋሚ ታሪኮች የተያያዙ በመሆኑ በመሃከሉ ጀባ አልኳችሁ እንጂ የአበበ የውድድር ወይም የስፖርት ታሪኩን ለማየት ስንሞክር በርካታ ጥሎ ያለፋቸው አሻራዎች እንዳሉ እንገነዘባለን። ዓለም-አቀፍ ውድድሮች ላይ በአሸናፊዎች መድረክ ላይ ባንዲራችንን ማውለብለብ የቻለው አቤ ዳግም ሌላ ህልም ነበረው። የሚጨበጥ ራእይ! በ1964 ላይ በጃፓን ሊደረግ ስለታሰበው የኦሊምፒክ ውድድር ላይ ለመሣተፍ ልምምዱን

ጠዋትና ማታ ያካሔድ ነበር። በርካታ አበበዎችም አፍርቷል። ተከትለውታልም። በሮማ ኦሊምፒክ የልፋቱን ዋጋ ከሐገሩ መንግሥት በትክክል ባያገኝም የላቀ ክብር አግኝቷል። ሞራሉ የበለጠ ተጠናከረ። ክብሩንም ላለማስነካት ለቶኪዮው የኦሊምፒክ ውድድር ዝግጅቱን አጠናቀቀ። የሰው ልጅ በሕይወት ዘመኑ እያለ ስንክሣር አያጣምና አበበም ታሞ ሆስፒታል ገባ። ሁናቴው የኢትዮጵያን ሕዝብ ቢረብሸውም ፈጣሪ ምሥጋና ይግባውና! አቤ የቀዶ ጥገና ሕክምና ተደርጐለት ወጣ። ወዲያውኑ ልምምዱን ጀመረ። ዝግጅቱንም አጠናቀቀ።
ይሁን እንጂ አበበ ያሸንፍ ይሆን? የሚለው ጥያቄ በበርካታ የስፖርት አፍቃሪዎች ዘንድ አከራክሮ ነበር። ከሆስፒታል በወጣ በ36ኛ ቀኑ የኦሊምፒክ ውድድር እጩ የሆነው አትሌታችን ውድድሩን ለመካፈል ወደ ጃፓን ዋና ከተማ ወደ ቶኪዮ በረረ። በነገራችን ላይ ይህች ውብ ከተማ የተቆረቆረችው በወንዝ ላይ ነው። አበበ ቶኪዮ ዓየር ማረፊያ ሲደርስ በከዘራ ተደግፎ ነበር። በዚህም ምክንያት ምእራባውያን ጋዜጠኞችና ተችዎች ኢትዮጵያ እንደማታሸንፍ በሰፊው አናፈሱ።
ከዚያ ቀደም ሲል የአበበን ሁናቴ በቅርብ ሆነው ይከታተሉ የነበሩ የዓለም ጋዜጠኞች እሱ ወደታከመበት ሆስፒታል ድረስ በመሄድ አጨናንቀውት ነበር። ውድድሩ እስኪደርስ ድረስ አበበ በተደጋጋሚ ቃለ-ምልልሶችን አድርጓል። ለቀረበለት ጥያቄ ሁሉ «አትጨነቁ፤ አሸንፋለሁ።» በማለት ነበር በሙሉ ልብ የሚመልስላቸው የነበረ። ጀግናው በቶኪዮ ለመሮጥ ያሰበው በጫማ ነው። ቶኪዮ በልዩ ልዩ ኅብረ-ቀለማትና በኦሊምፒክ ዓርማ አሸብርቃለች። የዓለም ሕዝብ በጉጉት ይጠብቀው የነበረው የኦሊምፒክ መዝጊያ ውድድርም እልህ Aስጨራሽና ወኔንና ጉልበትን የሚጠይቅ ነበር። ውድድሩ እንደተጀመረ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ተወዳዳሪዎች አንዱን ከአንዱ በማይለይበት ሁናቴ ማፈትለክ ጀመሩ። ቢሆንም ከመጀመሪያው አንስቶ የመሪነቱን ቦታ አበበ ብቻውን ተያይዞታል። እናም ቃሉን አላጠፈም። ዳግም የኦሊምፒክ ክብረ-ወሰን በመስበር ድልን ተቀዳጀ። በሮም ከተማ የሰበረውን ሰዓት በ2፡12፡15 አሻሻለው። ዓለም ዳግመኛ ጉድ አለ!።
የማይደገመው ተደገመ፤ ተደግሞ የማያውቀው የማራቶን ድል ተደገመ። ለአቤም እንዲህ ሲባል ተቀኘለት፤
ሮምን በባዶዕግሩ፤ ቶኪዮን በጫማ
ድል አድርጓል አቤ በሁለቱም ከተማ
ይህ ድንቅ አትሌታችን ክብሩን ጠብቆ፤ ታሪኩን ደግሞ፤ የሐገሩንም ሰንደቅ-ዓላማ ከፍ ብላ እንድትውለበለብ አደረገ። በዓለም ዙሪያ የመነጋገሪያ ርእስ ሆነ። እስከዛሬም ድረስ ቢሆን የዓለም ሕዝብ አበበን ጠንቅቆ ያውቀዋል።...

«ከ 1960 ጀምሮ የኦሊምፒክ ማራቶን የአውሮጳውያንና የአሜሪካውያን የግል ሃብት መሆኑ አበቃ። ከኢትዮጵያ ደጋዎች የተወለደ አንድ ሰው የሮማን የንጋት ውጋጋን ስሜት ፈጠረ። ይህ ያልታወቀ ሰው አበበ ቢቂላ ይባላል። ባዶ እግሩን ይሮጣል። ከአራት ዓመት በኋላ፤ ግን ጫማ አጥልቆ በድጋሚ ቶኪዮ ያሸንፋል»

ለአፍሪቃ፤ ለጥቁር ሕዝቦችና ለኢትዮጵያም የስፖርት በር ከፋችና ምሣሌ በመሆን ጀግናው አበበ በቶኪዮ ዳግም ድል አድርጐ ወደ ሐገሩ ተመለሰ። ከፍተኛ የክብር አቀባባልም ተደረገለት። ለእናት ሐገሩ ባለውለታነቱና ለራሱም ላጐናፀፈው ክብር፤ የልፋቱን ዋጋ ከሐገሩ መንግሥት ለማግኘት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ፊት ለሁለተኛ ጊዜ ቀርቦ የምክትል የመቶ አለቃነት ማእረግ ሹመት ተቀበለ። የማራቶን ጀግናነቱንም አረጋገጠ። ቀጣዩ ኦሊምፒክ ለአበበም ሆነ ለኢትዮጵያ በጣም አስፈለጊ ብቻም ሣይሆን ታሪካዊነቱም የላቀ እንደሚሆን ግንዛቤ እየያዘ መጣ። ቀጣዩ የኦሊምፒክ ውድድር ሊደረግ የታሰበው ከአራት ዓመታት በኋላ ሜክሲኮ ላይ ነው። ለአበበም ሆነ ለተከታዮቹ የሚታያቸው ራእይ ከውድድሩ በስተጀርባ ያለው ቁም ነገር ብቻ ነው። በተከታታይ ለሦስት ጊዜ ማሸነፍ ከቻሉ የማራቶን ንጉሥ የሚለው ክብር ማግኘት ነበር ለጥንካሬያቸው ተጨማሪ ግፊት። በነገራችን ላይ ለሦስት ጊዜ የኦሎምፒክ ማራቶንን በመከታተል ያሸነፈ እስከዛሬ የለም። ጀርመናዊው ሯጭ እንዲሁ እንደ አበበ ሁለት ኦሊምፒኮችን ብቻ ነበር በተከታታይ ያሸነፈው። እንደ ሕይወቴ ሩጫን እወዳለሁ። ሕይወቴም ሩጫ ናት (running is my life) ነበር ያለው። አበበ ብዙዎች አበበዎችን አፍርቷል። ብቻውን አይደለም። ማሞ ወልዴም ከኮሪያ ዘመቻ በድል ተመልሷል። ዋሚ ቢራቱ፤ ባሻ ፍቅሩ፤ በየነ አያኖም፤ የትነበርክ በለጠ፤ ሽብሩ ረጋሣ... እነዚህ ሁሉ ከአበበ የማይተናነሱ የዘመኑ ፈጣኖች ነበሩ። ቢሆንም የኢትዮጵያ ችግር «ምንጊዜም» አይጠፋምና በበጀት ምክንያት ሁሉም አይሄዱም። የምርጦች ምርጥ ይመረጣል። በ1968 የሜክሲኮ ኦሊምፒክ የምርጦች ምርጥ አበበና ማሞ በመሆን ተመረጡ። ጊዜው ሲደርስም ጉዞው ወደ ሜክሲኮ ሆነ፤ ከበዙ ሰዓት የዓየር በረራ በኋላ ሜክሲኮ ሲቲ ሲገቡ የኢትዮጵያም ሆነ የዓለም ጋዜጦች ርእሰ አንቀጽ ገፆችን አበበና ማሞ ሸፈኑት። ሁለቱም ምርጥ አትሌቶቻችን በአካልም በመንፈሰም ተዘጋጅተዋል። አበበ የኦሊምፒክ የማራቶን ንጉሥ ለመባል፤ ማሞም በበኩሉ የመጀመሪያ ውጤቱን ለማየት!። በሜክሲኮ ጥቂት ቀናት ቆይታቸውም ከአካባቢው ዓየር ጋር ለመተዋወቅ የልምምድ ፕሮግራምም ነበራቸው፤ በቀረው ትርፍ ጊዜያቸው ደግሞ ልዩ ልዩ ታሪካዊና መዝናኛ ቦታዎችን በመጐብኘት አሣለፉ። አይደርስ አይቀር የውድድሩ ቀን ደረሰ። ከሌሎች ተወዳዳሪዎች ጋር በመሆን የማስነሻውን ጥይት ተኩስ ይጠባበቃሉ፤ ውድድሩ ከተጀመረ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ጀግኖቹን አበበንና ማሞን የሚፎካከራቸው ጠፋ፤ የዕለቱ ዓየር ጠባይም ፀሃያማና ተስማሚ ስለነበር ተራ በተራ የመሪነቱን ቦታ ይቀባበላሉ። የውድድሩን ሂደት የሚከታተለውና የሚያስተላልፈው የሜክሲኮ ሬዲዬም ያለምንም ማጋነን የሁለቱን Iትዮጵያውያን በተለይም ደግሞ የAበበን ታሪክ አስመልክቶ ነበር ልዩ ትኩረት የሰጠው። ማሞንም በሚመለከት ከአራት ቀናት በፊት በ10ሺህ ሜትር የብር ሜዳሊያ ባለቤት የመሆኑን ታሪክ በሰፊው ያትታል፤ ውድድሩን በየተራ ለብቻቸው ይቀባበሉ ስለነበር ማን ያሸንፍ ይሆን? የሚል ጥያቄ መነሣቱ አልቀረም። ይሁንና ሁለቱም አትሌቶቻችን ከባዱን ጐዳና ተያይዘውታል። የውድድሩን የመጀመሪያ 25 ኪሎ ሜትር አገባደውታል።

በመሀሉ ማሞ ባልገመተውና ባላሰበው ሰዓት በጆሮው ተምዘግዝጐ የገባውን የአበበን ቃላት ማመን አቃተው። እንደመደንገጥ ብሎ «ምን አልከኝ?» በማለት ጠየቀው። አበበም የማሞን መደናገጥ ስለተገነዘበ እንደ ማባበል ዓይነት አለና «አይዞህ ታሸንፋለህ፤ እኔ አልቻልኩም፤ የእግሬ ወለምታ በጣም ተሰምቶኛል፤ ሌላም የማላውቀው ስሜት እየተሰማኝ ነው። ስለዚህ አደራዬን ተቀበለኝ፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይጠብቀናል፤ እኔ ስላልቻልኩ አንተ ቀጥል፤ የኢትዮጵያ አምላክ ይከተልህ» ካለው በኋላ አስፋልት ዳር ወደቀ። እውነትም በጣም ታሟል። ወዲያውኑ አበበ ሜክሲኮ ሆስፒታል በአስቸኳይ ተወሰደ። ማራቶን ልእልቷ አቤን ከዳችው። እርግጥ ነው በዚህ ውድድር የተጠበቀው አበበ ቢቂላ ነበር። የአበበ ውድድሩን ማቋረጥ ብዙዎቹን በማስደንገጡ በስቴዲየሙ የተገኙ ኢትዮጵያውያኖች የአበበ ማቋረጥ እንደተሰማ ስቴዲየሙን ለቀው ማሞ ወልዴን ለማበረታታት ወደ አደባባይ ወጡ። በዚያን ወቅት የነበረውን ሁናቴ ታዋቂው ጋዜጠኛ ሰለሞን ተሰማ እንዲህ ገልፆት ነበር፤ «የአበበን መውጣት ስሰማ ማሞን ለማበረታታት የጮህኩት ጩኸት ድምፄን ለሦስት ቀናት ያህል ዘግቶት ነበር።» ማሞ ብቻውን ቀሪውን ኪሎ ሜትር እየመተረ፤ በከፍተኛ ሞራል በመገስገስ ያለተቀናቃኝ የሜክሲኮን ኦሎምፒክ አሸንፎ የወርቅና የብር ሜዳሊያ ባለቤት ሆነ። ማሞ በዚህ የሜክሲኮ ውድድር የ10 ሺህ ኪሎ ሜትር ማጣሪያና ፍፃሜ ውድድርን ጨምሮ 62 ኪሎ ሜትር ከ195 ሜትር በመሮጥ የAንድ የወርቅና የአንድ ነሐስ ባለቤት በመሆን ብቸኛው ኢትዮጵያዊ ሣይሆን አይቀርም። አበበ ከሆስፒታል ወጥቶ ማሞን ባየ ጊዜ እጅግ ከመደሰቱም በላይ ስቅስቅ ብሎ ካንጀቱ አለቀሰ። «የኢትዮጵያ ሕዝብ ይጠብቀናል» ብሎት ስለነበር ማሞ ..ረውም። በሦስት ተከታታይ የማራቶን ውድድሮች ኢትዮጵያ የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት በመሆኗ ዓለምን ቢያስደንቅም የኢትዮጵያ ሕዝብ ደስታው ከመጠን በላይ ሆኗል። የቡድኑ አባላት ወደ አዲስ አበባ የተመለሱ እለትም አበበንና ማሞን ለመቀበል ሕዝቡ በነቂስ ነቅሎ ወጥቷል። እልልታው፤ ዘፈኑ፤ ዝማሬው፤ ጭፈራው የአዲስ አበባ ጐዳናዎችን ከማስጨነቁም ባላይ አዲስ አበባ ከመመሰቃቀሏ የተነሣ የሠርግና የደስታ አውድማ መስላለች። የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ በየአግጣጫው ይውለበለባል። የክብር ዘበኛው ባንድ ጀግኖቹን ለመቀበል በልዩና በሚያስደስት ቅንብር ያሣየው ትርኢት ድንቅ ነበር። እንዲህ ነው ጀግንነት! እንዲህ ነው ወንድነት! አበበና ማሞ አንድና ሁለት! በማለት እንዲህ ሲባል ተገጠመላቸው፤

ማራቶን ማራቶን ማራቶን ውዲቷ
አበበና ማሞ ሆነዋል ባለቤቷ
ማራቶን ጠብቀሽ አቤን ብትቆጪ
ሆኖም አልቀረልሽ የትም አታመልጪ
አበበ ቢወጣ በእግር ወለምታ
ማሞ ተተክቷል የሐገሩ መከታ
ሮምን በባዶ እግሩ ቶኪዮን በጫማ
ድል አድርጓል አቤ በሁለቱም ከተማ
ተባለላቸው፤ ተዘመረላቸው። ተጨፈረላቸውም።

አበበ አንደ ዛሬ የዘመኑ ሥልጣኔ ባልተስፋፋበት ጊዜ በባዶ እግሩም፤ በጫማም የኦሊምፒክ ውድድርን ብቻ ሣይሆን በተለያዩ ውድድሮች አሸንፏል። ከዋሚና ከማሞ ጋርም ብዙ የዓለም-አቀፍ ውድድሮች ላይ ተካፍለው አሸንፈዋል። በዚያን ጊዜ አበበ የገባበት ሰዓት ዛሬም ቢሆን በቀላል Aይገባም። አበበ ቁመቱ ሎጋ፤ የቀይ ዳማና መልከ-መልካም Iትዮጵያዊ ነበር። በመልኩና በቁመናው እንዲሁም ባስመዘገበው ውጤት በመላው ዓለም ትልቅ ስምና ክብር አግኝቷል።
ከዚህ ውድድር በኋላ የጀግናው ሕይወት እንዴት ነበር የሚል ጥያቄ አንባቢያን ሊሰነዝሩ ይችላሉ። አበበ የጀግንነት ክብር ማግኘቱ፤ ዝናና ታዋቂነት ማትረፉ፤ በአጠቃላይም ስሙ በሐገር ውስጥም ይሁን በዓለም አቀፍ ደረጃ ጐልቶ ይታወቅ እንጂ በሕይወት ዘመኑ በርካታ ፈተናዎች ውስጥ ገብቷል። ዝነኛ ሰው ብዙ ችግሮች አጋጥመውታል። ቅናት እና ፍቅር ዋነኛዎቹ ናቸው። አበበም ከሁለቱ ለማምለጥ አልቻለም። ጀግና ይወደዳል፤ ይፈቀራል፤ ይከበራል። በ1972 ዓ.ም. በጀርመን ሙኒክ ከተማ የተካሄደው የማራቶን ውድድር ለኢትዮጵያውያኖች መጨረሻ ድል ነበር። አበበ ቢቂላ በሙኒክ ከተማ የተገኘው እነዚያ የሚወናጨፉ እግሮቹን ጣጥፎ፤ በተሽከርካሪ ወንበር ላይ (1) ሲሆን፤ በስታዲየሙ የተገኙ ተመልካቾች ከመቀመጫቸው ተነስተው በጭብጨባ ነበር ተቀበሉት። በዚሁ በሙኒክ ውድድር በAርባ ዓመት እድሜው የተሣተፈው ማሞ 2፡14፡31 በመግባት 3ኛ ወጥቶ የነሐስ ሜዳሊያ ተሸላሚ ለመሆን በቃ።

(2)

በነገራችን ላይ በሙኒኩ ውድድር Iትዮጵያ በማራቶን ነሐስ ሜዳሌያ ከማግኘቷ ሌላ በ10ሺህ ኪሎ ሜትር በአትሌት ምሩፅ ይፍጠር አማካይነት ሁለተኛውን ነሐስ አግኝታለች። ግናው አበበ ቢቂላ በተሽከርካሪ ወንበር ላይም ሆኖ በድጋሚ የዓለም የቀስት ሻምፒዮን ሆኗል። በእግሩ ያጣውን የወርቅ ሜዳሊያ በዓይኖቹና በእጆቹ ለማግኘት ችሏል። በ1966 ዓ.ም. አቤ ለዘላለም ይለየን እንጂ። ሻምበሉ ምን ጊዜም ሕያው ነው። ስሙ ከመቃብር በላይ ነው። አበበ ዛሬም ለሚሊዮን ኢትዮጵያውንና ሌሎች አትሌቶች አርዓያና «Inspiration» ምንጭ በመሆን በርካታ አበበዎችን ተክቶልን አልፏል። የዚህ እውቅና ድንቅ አትሌታችን የክብር መታሰቢያ ሐውልት በባእድ ሐገር በቶኪዮ በክብር ከመቆሙም በላይ ልዩ እንክብካቤም እንደሚደረግለት አንባቢያን እንዲገነዘቡልኝ እሻለሁ። በሐገራችን ያለው የአበበ ሐውልት ጉዳይ ግን እጅግ አሣዛኝ ነው። አቶ አቤ ሴሎም በክብር ያሠሩለት ሐውልት ዛሬ ምን እንደሚመስል ለአንባቢያን እተዋለሁ። በመጨረሻም ኢትዮጵያ ከ1972 ዓ.ም. በኋላ ለማራቶን ድል ባትታደልም በተሣተፈችባቸው ኦሊምፒኮች ሁሉ የሩጫን ድል Aላጣችም። በ10ሺህና በ5ሺህ ኪሎ ሜትር ውድድሮች ብርቱ አትሌቶች ድል አጐናፅፈውታል። ምሩፅ ይፍጠር፤ መሐመድ ከድርና ቶሎሣ ቆቱ በ10ሺህ፤ መሐመድ ከድር፤ ዮሐንስ፤ ምሩፅ ይፍጠርና እሸቱ ቱራ የቡድን ሥራ በመሥራት በ5ሺህ ኪሎ ሜትር ተከታትለው በመግባት ሞስኮ ላይ ታሪክ ሠርተዋል።

ኢትዮጵያ በ1992 ዓ.ም. በስፔን ባርሴሎና በተካሄደው ውድድር በደራርቱ ቱሉ በ10ሺህ፤ በፊጣ ባይሣና በአዲሱ አበበ 1የወርቅና 2 የነሐስ አግኝታለች።1996 ዓ.ም. በአትላንታ ኦሊምፒክ ኃይሌ ገ/ስላሴ፤ ጌጤና ፋጡማ ሮባ በድል አንበሽብሸውናል። ንጉሱ በንግሥት ተተካ። በአትላንታ። አበበ የባረከውን፤ ማሞ የደገመውን የማራቶን ድል Aትሌት ፋጡማ ሮባ አፀናችው። ኢትዮጵያ በወንዶች ብቻ ሣይሆን በሴቶች ማራቶን እንደገና ንግሥት ሆና ብቅ አለች። በአበበ ቢቂላ ፈር ቀዳጅነት ጥቁር ሕዝቦችን ያኮራው የማራቶን ድል በማሞ ወልዴ አርማ አንሺነት የፀደቀው የማራቶን ድል፤ ዛሬ ከማንም በላይ ለኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያዊያት ሁሉ ተናፋቂ ነው። በሚቀጥለው ተረኛ ባለታሪክ እስከምንገናኝ ድረስ ቸር ይግጠመን።

የግርጌ ማስታወሻ
በዘመኑ በIትዮጵያ ራዲዬ እንደተነገረው አበበ ሸኖ በምትባል አካባቢ መኪና ተገልብጦ አደጋ ደረሰበት የሚል ዜና ተሠራጨ። በእውነት አበበ የሚኪና አደጋ ነው የደረሰበት? እንዴት ሁለቱን ፈጣን እግሮቹን ብቻ Aደጋ ደረሰባቸው? ዓይኑ አልተነካ፤ እጁ ላይ ቁስል አልደረሰበት። ምንድነው ምስጢሩ? እስካሁን ድረስ ለኢትዮጵያ ሕዝብ የአበበ አሟሟት ትክክለኛ መንስዔ በትክክል ካለመታወቁም ባለይ እንቆቅልሽም ሆኖ ይገኛል። የአሟሟቱ መንስዔ የተሣፈረባት ቮልስቫገን ሣትሆን «ልዩ እጅ» የነበረው ስለመሆኑ በጊዜው ልንሰማ ችለናል።
ሶራ ጃዌ
.
ሮም የኢትዮጵያ ደመኛ አገር የነበረችዋ የጣሊያን ዋና ከተማ ናት። በሮም፣ ቤኒቶ ሙሶሊኒ ኢትዮጵያን በወረረ ጊዜ፣ በአዲስ አበባ የጣሊያን ባንዲራ በመተከሉና ኢትዮጵያ በጣሊያን እጅ በመውደቋ የድንፋታ ንግግር ለአገሬዉ ሕዝብ ያደረገበት ከተማ ናት። ከሃያ ስድስት አመታት በኋላ፣ እንደ ኢትዮጵያዉያን አቆጣጠር በ 1952 ዓ.ም ባንዲራችን መሬት ወድቆ ጮቤ በተረገጠባት ከተማ የኢትዮጵያ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ባንዲራ ከፍ ብሎ ተዉለበለበ። በዚያን ቀን ታሪክ ተሰራ።


domenica

በፖስታ ቤት የደረሰኝ ወረቀት የወጡ እስከ 30 10 07 ድረስ መመለስ ነበረባቸው


06 11 07
ውደ ድሮው ሕግ ተመለሰን።
ከእንግዲህ ወዲህ በደረሰኝ ወረቀት ብቻ ከጣሊያን መውጣት አይቻልም። የወጡም ተመልሰው መግባት አይችሉም።
የመመሪያው ማሻሻያ ነጥብ ጊዜያዊ ነበር።
.
በጣሊያን የመኖሪያ ፈቃድ እስከሚታደስላቸው በመጠባበቅ ላይ ለሚገኙት የውጪ ሀገር ዜጎች የሀገር ውስጥ አስተዳደር ሚኒስትር አውጥቶ የነበረው ወደ ትውልድ ሀገራቸው ደርሶ መመለስ የሚያስችለው ጊዜያዊ መመሪያ የቀን ገደብ እንደነበረው ይታወቃል። ይኸውም እስካለፈው ወር መጨርሻ ላይ ማለትም አስከ 30 10 2007 ድረስ ነበር። በወጣው መመሪያም ላይ ይህ የጊዜ ወሰን ተጠቅሶ እንደነበረ ይታወቃል። ይኸውም የሚያስረዳው “የሶጆርኖ መታደስን ለሚጠብቁ ለዚህም መጠባበቂያ የፖስታ ቤት ደረሰኝ ያላቸውና በጉዞ ላይ የነበሩ በሙሉ ይኼ ቀን ሳያልፍ መመለስ ይኖርባቸዋል” የሚል ነበር። ስለዚህ የሶጆርኖ ታዳሽ ተጠባባቂ ሆነው ከጣሊያን የወጡ ከሆነ የመመለሻቸው የጊዜ ገደብ ቀን ሳይወድቅ የተመለሱ መሆን ይኖርባቸውል ማለት ነው።
ማሳሰቢያ
ከእንግዲህ ወዲህ በደረሰኝ ወረቀት ብቻ ከጣሊያን መውጣት አይቻልም። "በደረሰኙ ፈቃድ የወጡና አስከሚመለሱ ድረስ የቀኑ ገደብ ያለፈባቸው ተመልሰው መግባት ይችላሉ ወይ?" ለሚለው ጥያቄ መልሱ "አይችሉም" ይሆናል።......
.
.
Rientri col cedolino Non si passa più per l'Ue
06 11 07
Finite le agevolazioni, si ritorna alle vecchie regole
ROMA - Niente più tappe europee per chi aspetta il rinnovo e vuole viaggiare tra l'Italia il suo Paese d'origine: il 30 ottobre è scaduto l'accordo temporaneo che permetteva a chi aveva con se passaporto, permesso scaduto e cedolino di fare scalo in tutti gli aeroporti e in alcuni porti dell'Ue. Sono così ritornate in vigore le vecchie limitazioni: uscita e reingresso in Italia dallo stesso valico di frontiera e viaggio che non preveda il transito in altri Paesi Schengen. Bisogna inoltre portare con sé il passaporto e la ricevuta dell'ufficio postale, che verranno timbrati dalla polizia sia all'uscita che al reingresso in Italia.
Regole simili sono in vigore anche per chi è arrivato con i flussi o con un ricongiungimento familiare ed è ancora in attesa del primo permesso di soggiorno per lavoro. In questo caso però, dal momento che non si ha un permesso, bisognerà esibire alla frontiera anche il visto rilasciato dal consolato che specifica il motivo del soggiorno in Italia.
(6 novembre 2007) Elvio Pasca


venerdì

Cucina Etiope


SAPORI D'ETIOPIA

di Abraham Zewdie

In Etiopia il pranzo inizia con un tipico rituale, il lavaggio delle mani. A tavola viene portata un brocca di metallo o terracotta contenente acqua, la quale viene versata sulle mani degli ospiti. Subito dopo viene servita la prima portata, un leggero piatto di fermenti o siero di latte seguito da specialità piccanti.
In Etiopia, la dieta è scandita dai lunghi periodi di digiuno previsti dalla religione copta, a cui fanno seguito periodi in cui la carne diventa la base principale dei pasti. E, da non scordare, il caffè è originario della provincia del Kaffa, da dove prende il nome, e in Etiopia bere questa bevanda è un vero e proprio rito. Se ne avete la possibilità prendete parte a questa cerimonia, gustando il caffè che verrà servito per tre volte in piccole tazzine di ceramica, e per una volta fate si che il tempo non vi corra dietro, e prendetevi tutto il tempo necessario per partecipare a una cerimonia il cui ricordo vi rimarrà sicuramente molto impresso.
Molti altri piatti lasciano nel visitatore una impronta indimenticabile. Sono preparate in occasione della nostra festa e sono da assaggiare, non appena se ne presenta l'occasione.

Piatti tipici ed Elementi base

INJERA - Pane lievitato e spugnoso sul quale si servono quasi tutti i piatti, simile ad una cialda ricavato ad una miscela di Teff, (un ceriale locale ed acqua.) Avete presente quella sottile sfoglia di gommapiuma che riveste i vostri preziosi regalini - tipo Swarowsky - che volete proteggere dagli urti? Ecco: Ingera è una sfoglia di pasta di miglio molto simile ma un po' più sottile e di un color grigio-chiaro e grigio spento. Riveste l'interno del gran piatto da portata, da cui tutti dovranno attingere, che contiene, al centro, mucchietti di saporita carne di montone o di bue, circondata da salsine multicolori, ma tutte tremendamente piccanti. L'injera è disposta a fette sopra i Mesob, cioè (speciali supporti di paglia colorati, decorati finemente ed intrecciati.) Parti diverse di Wot sono disposte artisticamente sulle fette del Injera, nel mesob. Spesso il pranzo non cominicia finchè il padrone di casa non spezza, per ogni uno dei comensali, una porzione di Injera.
Le buone maniere del luogo insegnano che questo piatto vada mangiato rigorosamente con le mani. Staccate con tre dita un pezzo di 'Ingera, tanto per intenderci quella che sembra una sfoglia di gomma piuma, fatene un piccolo fazzoletto, poggiatelo delicatamente sui pezzettini di carne e poi, stringendo i quattro polpastrelli, a cui avrete avuto l'accortezza di opporre l'ultimo dito della vostra mano, il pollice, fate in modo di pescare uno o più pezzettini di carne, imbevetelo in una o più salsine e, finalmente, portate il tutto alla bocca. Ripetere l'operazione fino a sazietà.
Sembra difficile ma non lo è; Se tutto questo vi sembra complicato- in parole povere "quello che bisogna fare è staccare un pezzo di Injera e arrotolarlo ai pezzeti di carne di Wot. Vi si oppongono, però, atavici tabù che riaffiorano e cui bisogna strenuamente opporsi: quante volte da bambini c'è stato, infatti, affermato che non bisogna mangiare con le mani?

LA RICETTA D'INGERA
Impastare 5 etti di farina 00, 5 etti di farina gialla di mais (quella da polenta), 250 grammi di semola di grano duro, 25 grammi di lievito e 1 bicchiere d'acqua in una ciotola capiente. Coprire e far riposare a temperatura ambiente 3 giorni se inverno, 2 se estate. Lavorare l'impasto fermentato con acqua sufficiente a farlo diventare fluido - circa 3 bicchieri. Scaldare una padella antiaderente e versare a filo il composto, uno strato di 3-4 millimetri, come per una crepe. Quando inizia a rapprendere devono comparire le bollicine che danno la caratteristica consistenza spugnosa al pane. Coprire e lasciare cuocere per circa 3 minuti, evitando che prenda colore. Lasciar raffreddare su un canovaccio evitando di sovrapporre le focaccette finche' non sono fredde.

Il WOT
Una sorta di stufato di piccante, un miscuglio di carne, in una saksa di cipolle e spezie. Il sapore infuocato del wot è dato dal berbere, una mistura di peperoncino, aglio, chiodi, di garofano, coriandolo, ginger fresco. Il wot è accompagnato inevitabilmente dall'ingera. Piccante ma deliziosissimo.

LA RICETTA DI "SEGA' WOT" PER 4 PERSONE
(stufato di manzo, kibe, cipolla e berberrè)
Fare appassire coperti 1 grossa cipolla tritata e 2 spicchi d'aglio tritati. Dopo 5 minuti aggiungere 1 cucchiaio di burro chiarificato, 3 cucchiai di berbere' - e' forte come il veleno - 1 bicchiere d'acqua, sale. Fare restringere lentamente, poi aggiungere 500 grammi di pelati ed eventualmente un altro bicchiere d'acqua. Continuare a sobbollire per 1/4 d'ora, poi aggiungere 500 grammi. di manzo a cubetti. Finire di cuocere per 1 oretta, finche' la carne e' cotta e il fondo ristretto. Si mangia tradizionalmente sopra l'injera (pan di spugna), in modo che questo si imbeva di sugo. Oltre con il carne di manzo il Wot puo essere preparato con altri carne di qui il sapore viene anche diverso altrettanto sono molto gustose.

PIATTI DI CARNE

DORO WOT (stufato di pollo e uova, kibe, cipolla e berberrè)
BEG WOT (stufato di pecora, kibe, cipolla e berberrè)
BEG ALICHA' (Stufato di pecora, Kibe, Cipolla, e Berberie )
ALICHA' (stufato di pecora, kibe, cipolla senza berbrrè ma con verdure cotte aromatizzate) E' un piatto gustoso a base di agnello o puo essere preparato anche di manzo, insaporito da cipolle e ginger verde. E' molto meno focoso del wot. Un miscuglio di carne in una salsa di cipolle e spezie
KITFO (carne cruda tagliata a piccoli pezzi e berberrè, kibe, e spezie. il "burundo di carne cruda
TEBS (carne cotta con cipolla, kibe e peperoncino fresco)

PIATTI CON VERDURE ED AROMI

ALICHA' (stufato di verdure miste cotte in una salsa di cipolle e spezie)
MESSER WOT (stufato di lenticchie in una salsa di cipolle e spezie)
GOMMEN WOT (stufato di bietola in una salsa di cipolle e spezie)
ATER WOT (stufato di piselli in una salsa di cipolle e spezie)
SCIRO' WOT (crema di piselli in una salsa di cipolle e spezie)
BERBERE (polvere di peperoncino, aglio e altri aromi dal colore rosso vivo e molto piccante)

FORMAGGI
AIB (formaggio preparato con latte di mucca)
KIBE (Burro preparato con latte di mucca, aglio e zenzero, dal forte odore speziato)

BEVANDE

VINI (bianchi e rossi molto aromatici di produzione locale Guder, Dukam, Axum)
BIRRE (di produzione locale Bedele, Harar)
TEJ (idromiele - fermentato di luppolo e miele )
TALLA (La bevanda locale fermentato di cereali simile a birra a base di orzo e erbe aromatiche)
ARAKE' (grappe aromatizzate )
BUNNA (caffè tostato, macinato e preparato al momento di essere servito)

ANTIPASTI E DOLCI VARIE

DABO KOLO (CHICCHI DI PANE DOLCE FRITTI E COLORATI)
SAMBUSA (FAGOTTINI DI PASTA FRITTI RIPIENI CON CARNE OVERDURE E PEPERONCINO FRESCO)SAPORI D'ETIOPIA

di Abraham Zewdie


የሀገራችን ባህላዊ ምግቦች አሠራር


እህቶቼ ወንድሞቼ ... በዚህ ገፅ ላይ በተለያዩ አርዕስት ላይ አስተዋፅዖ ማድረግ ይችላል ስለተባለ እኔም እስቲ ሙያዬ በሆነው ልካፈል ብያለሁ። ያው የምታውቁትን አንዳንዱን የሀገራችን የምግብ አሰራር እንዴት እንደሆነ በጽሁፍ ልማቅረብ ፈልጌ ነው። ይህም እኮ ቢሆን ባህላችንን ለማሳየት ይጠቅማል። አይደለም እንዴ? ምቼም እናንተም ወንዶችም ብትሆኑ የሴት ስራ ብላችሁ ከማንበብ እንደማትቆጠቡ ተስፋ አደርጋለሁ:: ለምሳሌ "የምስር ወጥ እንዴት ተደርጎ ነው የሚሰራው?" ብዬ ብጠይቃችሁ "ከምስር ነው" እንደማትሉኝ ተስፋ አደርጋለሁ:: እኛ ምን አገባን ፓስታና መኮረኒ እያለ፣ እኛ ምን አገባን ሩዝ እያለ ካላችሁም መልካም ነው:: ለማንኛውም የአሰራሩን፣ ቅደም ተከተሉን፣ የእሳቱን መጠን፣ የምስሩን መጠን፣ የጨዉን መጠን፣ ወዘተ... ተጠንቀቁ:: ይህንንም ለሴተ ላጤዎችና ለወንድ ላጤዎች ነገሩ እንዲገባቸው በዝርዝር ለማስቀመጥ እሞክራለሁ።
.
ያበሻ ጎመን በበርበሬ
.
* መጀመሪያ ጎመኑ በጣም ደቆ ይከተፋል ::
* ከዚያም በብረት ድስት ወይም ሸክላ ድስት (እዚሁ ጣሊያን ሀገር ከተገኘ) በደንብ ታጥቦ ይጣዳል ::
* ጎመኑ ብቻ ድስቱ ዉስጥ ይገባና በደንብ ተከድኖ እንዲበስል ይደረጋል :: (አስታዉሱ ምንም ዉሀም ሆነ ሌላ ነገር አይገባበትም በደረቁ ነው ... የራሱ ዉሀ ስላለው በንፋሎትና በራሱ ዉሀ ይበስላል :: እንዲበስል የእሳቱ መጠን እኔ በጋዝ ስለምሰራ .. እንዳያር በጣም መከፈት የለበትም ለሰስ ያለ መሆን አለበት :: እሳቱ ከበዛ የስሩን ቶሎ ያሳርረዋል እረጋ ሲል ግን እንፋሎት እንዲኖረው ይረዳል :: ከ20 ደቂቃ በሁዋላ ከፍቶ ማማሰል ያስፈልጋል ..ከአረንጓዴነቱ ወጥቶ ጠቆር ያለ አረንጓዴ ከሆነ በስሏል ማለት ነው)
* ድስቱን አዉጥቶ ጎመኑን በሌላ ሰሀን መገልበጥ
* ሽንኩርት ድቅቅ አድርጎ መክተፍ (ትልቁ ከሆነ 2 ራስ ሽንኩርት ይበቃል)
* ነጭ ሽንኩርት ግማሽ ራስ አድቅቆ መክተፍ (መፈጨት የለበትም)
* ድስቱን ጥዶ መጀመሪያ ቀይ ሽንኩርትና ዘይቱን በጣም እንዳይሞት አድርጎ መጥበስ
* ከዚያም በርበሬ ሳይበዛ ጨመር አድርጎ ማቁላላት
* ጎመኑን መቀላቀልና ማዋሀድ
* ቀጥሎ ነጭ ሽንኩርቱን መጨመር
* በመጨረሻ ለጋ የበሻ ቅቤ ትንሽ ጣል አድርጎ ካዋሀዱ በሁዋላ አዉጥቶ ትንሽ ቅምስ ማድረግ።
አቤት ሲጣፍጥ!! ስትፈልጉ እዚሁ በፓዴላ ላይ በምንሰራው እንጀራ ወይም በዳቦ መብላት ነው። አደራችሁን እጃችሁን እንዳትቆረጥሙ ታዲያ::
ሌላ የምግብ አሠራር ይዤ እስከምቀርብ እስቲ ይመቻቸሁ እላለሁ።
Marta Pedrini
.
የዶሮ አሰራር
.
አብዛኛዉ ሰው ሲሰራ ያየሁት ሁሉንም በተራ እያስገቡ ሲያበስሉ መዋል ነው:: ከዛ ይልቅ አጠር ያለ መንገድና የሚጣፍጠው::
* ለ1 ዶሮ 3 ኪሎ ሽንኩርት በጣም ደቆ ይከተፋል
* ሁለት ራስ ነጭ ሽንኩርትና ዝንጂብል በጣም ሳይበዛ መፍጨት ... (ዝንጂብሉ ሳር ነገር እንዲኖረው መሆን የለበትም። በደንብ ይድቀቅ)
* የተከተፈዉን ሽንኩርት ከሩብ ሊትር ዘይት ጋርና ጨው ጨምሮ ድስቱ ዉስጥ አስገብቶ በደንብ መግጠምና መጣድ (ምንጊዜም ወጥ ሲሰራ ሳት መብዛት የለበትም)
* ከ15 ደቂቃ በሁአላ መክፈትና ማየት (እርግጠኛ ነኝ ሽንኩርቱ በደንብ ሙሽሽ ብሎ ይበስላል)
* ከዚያም በርበሬ ወይም ድልህ መጨመር (ሁለት ጭልፋ (የወጥ ማዉጫ ማንኪያ ) ትልቅ ጭልፋ መሆን የለበትም መካከለኛው ይበቃል)
* ከዚያም በደንብ እጅ ሳይቦዝን እያማሰሉ እንዳያር ማማሰል ... በደንብ ከለሩ ወደ ደማቅ ቀይ ሲሆን የተገነጣጠሉትን ዶሮዎች አብሮ ማዋሀድና ከድኖ ማብሰል ::እንዳያር በየጊዜው እየከፈቱ ማገላበጥ ::
* የተፈጨዉን ነጭ ሽንኩርትና ዝንጂብል ማስገባት :: ከዚያም የማዉጫ ዉሀ በጣም እንዳይቀጥን ሆኖ መጨመር ::
* እጥር ምጥን ሲል ማለትም ዉሀዉን ሲመጠው እና ሲማሰል ለድለድ ሲል ቅቤ በጭላፋ ዛቅ አድርጎ መጨመርና ማዋሀድ ከዚያም ማዉጣትና እስኪበርድ መጠበቅ
* የተቀቀለ እንቁላል ከላጡ በሁዋላ በሹካ ወጋ ወጋ አድርጎ ወጡ ዉስጥ ቢቀላቀል የበለጠ የዶሮ ባህላዊውን አሰራር ያጎላዋል::
. ... ከዚያማ አቤት አቤት!! ... ስንት ጊዜ "እጂሽን ለወርቅ እንጂ ለእሳት አይበለው" ተብዬበታለሁ መሰላችሁ!!
Marta Pedrini
.
የክትፎ አሠራር
.
1ኛ. ብዙን ጊዜ ለክትፎ ስራ የቂቤው አይነት እና የቂቤው አነጣጠር በጣም ወሳኝነት አለው። ነገር ግን ሁሉም እንደፍላጎቱ ቅቤውን ሊያዘጋጅ ይችላል። በብዛት ግን ያልበሰለ እና ለጋ ቂቤ ይመረጣል። 2ኛው አስፈላጊ ነገር የሚጥሚጣው አዘገጃጀት ነው።3. የስጋው አይነት ቀይ ስጋ በተቻለ መጠን ዉሀ እንዳያዝል ትኩስ ስጋ ቢሆን ይመረጣል .. በ እጅ ወይም በማሽን ከተከተፈ በሁአላ .. በዉስጡ ያለውን ስራስር እናነጭ ስጋ ለቅሞ ማውጣት ያስፈልጋል። እንዲሁም ስጋው በማሽን ከተከተፈ .. ሊያያዝ ስለሚችል .. ከተከተፈ በሁላ የተያያዘ ስጋ ካለ መበታተን .. አስፈላጊ ነው። አዘገጃጀቱ ፡-
በመጀምሪያ በዝርግ መጥበሻ በጣም በዝቅተኛ እሳት .. ለግማሽ ኪሎ ስጋ ... ወደ 3ጭልፋ ቂቤ ማቅለጥ (እንደፍላጎት ማድረግ ይቻላል ) ... እና እዚያው የቀለጠው ቂቤ ላይ ሁለት የሾርባ ማንኪያ ሚጥሚጣ እና ግማሽ የሾርባ ማንኪያ የተፈጨ ጨው አድርጎ መቀላቀል .. እሳቱ ሳይበዛ ቂቤውን ለማቅለጥ ብቻ መሆን አለበት.. ቅቤው ነንደቀለጠ እና እንደተዋሀደ መጥበሻውን ከሳት ላይ አዉርዶ ስጋውን ጨምሮ በጣም በፍጥነት መለወስ ወይም መታሸት ይኖርበታል። ከዚያ ወደ ማቅረቢያ እቃ ዉስጥ ገልብጦ ማቅረብ። ታዲያ ምን ያደርጋል! እዚህ አይቻልም እንጂ ቢቻል በቆጮ ነበር ... ከጠፋም ያው በfarina እንጀራችን ... አደራ .. እንግዲህ ሙያ እንደየቤቱ ይለያያል ... መልካም ክትፎ
Marta P.
.
ቀይ የስጋ ወጥ
.
(ለ4 ሰው የሚሆን የሚያስፈልጉን)
- 3ራስ ቀይ ሽንኩርት
- 1ራስ ነጭ ሽንኩርት
- ዝንጅብል (እንዳስፈላጊነቱ )
- ኮረሪማ፣ ጥቁር/ነጭ ቅመም የመሳሰሉት
- ግማሽ ኪሎ ስጋ (በሚፈለገው መንገድ ሳያንስ እና ሳይተልቅ መክተፍ ):
- 2 የሾርባ ማንኪያ በርበሬ :
- 2 የበሰለ ቲማቲም :
- ጨው እና ዉሀ .. ዘይት
አሠራሩ
1. የተከተፈውን ቀይ ሽንኩርት በ መካከለኛ እሳት ላይ ከድኖ መጣድ እና ሽንኩርቱን ለ3-5 ደቂቃ በ እንፋሎቱ እንዲበስል ማድረግ
2. ቲማቲሙን አንዴ በፈላ ዉሀ ገንፈል ካደረግነው .. እንዲላጥልን ከሆነ .. በሁላ ቲማቲሙን ልጦ .. ከትፎ ሽንኩርቱ ላይ መጨመር እና ለ2/3 ደቂቃ ከሽንኩርቱ ጋር ማዋሀድ
3. ከዚያ ዘይት ጨምረን ታሁንም ከሁለት ደቂቃ በሁላ 2 የሾርባ ማንኪ በርበሬ ጨምሮ (አሁን ዉሀ አይኖረውም ሽንኩርት ቲማቲም እና ዘይት ብቻ ነው ነንፋሎቱ ስለሚወጣ ) ለ5ደቂቃ በርበሬው እንዳያር ቶሎ ቶሎ ማማሰል እና .. ዉሀ ጠብ እያደረጉ ለተወሰ ደቂቃ ማብሰል ..
4. አሁን ከትፈን ያዘጋጀነውን ስጋ መጨመር እና አሁንም ዉሀ ሳይኖረው በደረቁ በዘይቱ እና በበርበሬው እንዲጠበስ ማድረግ ስጋውን .. ድስቱን ግን እየያዘ ካስቸገረን ዉሀ ጠብ እያደረጉ ለ 10 ደቂቃ ስጋውን ከ ቁሌቱ ጋር በደንብ ማብሰል .. እና የተፈጨ ዝንጅብ እና ነጭ ሽንኩርቱን ጨምረን አብረን ማብሰል .. ከዚያ ስጋውን በ 15 ደቂቃ በደረቁ በቁሌቱ ካበሰልን በሁላ 5. አንድ ሌትር ዉሀ ከልሰን ለ10 ደቂቃ እሳቱን ጨመር አድርገን ማንተክተክ ..ጨውም እንደሚፈለገው መጠን (1 የሻይ ማንኪያ ) እና እንደ መከለሻ .. ጥቁር /ነጭ ቅመም መጨረሻ ላይ መጨመር ... ሊወጣ ሲል ወይም ከ ቁሌቱ ጋ ዉሀ ሳንከልስ ሁለት የሾርባ ቂቤ ብንጨምርበት ሸላይ ይሆናል .. ወጡ በደንብ ከበሰለ .. አረፋ ነገር አይኖረውም ... ስለዚህ ዉሀ ከጨመርን በሁአላ ለ 15 ደቂቃ አብስሎ ማውጣት ..
ከዚያማ በቃ ከዛማ በእንጀራ ማገላበጥ ነው ... ቢቻል መጎራረስ !
.
የበግ ዱለት ለ4 ሰው
.
* ጨጓራዉ በደንብ ንጹህ እስከሚሆንና ሽታዉ ጭራሽ እስኪጠፋ መታጠብ አለበት ከዚያም አንጀቱንና ጨጓራዉን ዉሀ ጥዶ ገንፈል ማድረግና ማዉጣት
* ከዚያም ጥቁሩ ጨጓራ ጸጉሩ መገፈፍ (መፋቅ ) አለበት አንዳንድ አንጀቶች ዉስጥም መዉጣት ያለበት አለ እሱን እየላጉ ማዉጣት ከዚያም በጣም አድቅቆ መክተፍ
* ሌሎቹ የዱለት ክፍሎች እንደ ልብ ኩላሊት እና ጉበት ንጹህነታቸው ታይቶ በደንብ ጸዳድተው ደቀው ተከትፈው በንጹህ ሰሀን ይቀመጡ
* ሁለት ራስ ሽንኩርት የፈረንጅ ሽኝኩርት ነው በደንብ ደቆ ይከተፋል
* አንድ ራስ ነጭ ሽንኩርት አይፈጭም ደቆ ይከተፍ
* ሁለት ረጃጅም የሚያቃጥሉ ቃሪያዎች በደንብ ደቀው ይከተፉ
* ብረት ድስት መጣድና ሳቱን ለሰስ አድርጎ ከፍቶ ዘይቱ ሳይበዛ ከቀይ ሽንኩርቱ ጋር አድርጎ በጣም እንዳይሞት አድርጎ ጠበስ ማድረግ ከዚያ ላይ ነጭ ሽንኩርቱን መጨመር አስታዉሱ ዉሀ አይገባበትም
* ከዚያም ሳይከደን መሰል መሰል አድርጎ ደቆ የተከተፈዉን ጨጓራና አንጀት መጨመር ከ 2 ደቂቃ ማማሰል በሁዋላ ሌሎቹን የዱለት ነገሮች መጨመር አብረው ለብ ሲሉ እያማሰሉ ወዲያው አንድ የሾርባ ማንኪያ ሚጥሚጣ የደቀቀዉን ቃሪያና ለጋ ቅቤ ጣል አድርጎ ማዋሀድና ወዲያው ማዉጣት
ታዲያ በመጀመሪያ ለሴት ስይሆን ለወንድ ልጅ ማጉረስ ወንደ ላጠዎችና ሴተ ላጠዎች አስቡበት ትዳር መመስረትን በዚህች አለም ላይ ጥሩ ስምንና ራስን ተክቶ ማለፍ ነው ትርፉ ሌላ ምንም የለም!
Marta P.
.
የበግ አልጫ
.
2 ራስ ሽንኩርት የተከተፈ በዘይት ማቁላላት ከዚያም የተቆራረጠውን የበግ ስጋ ጨምሮ ካለ ውሀ ለስለስ ባለ እሳት ማቁላላት
- ቀጥለውም ትንሽ ውሀ ጠብ እያደረጉ ማማሰል ትንሽ ጠየም ማለት ሲጀምር ውሀ መጨመርና እሳቱን ትንሽ ከፍ ማድረግ
- መንተክተክ ሲጀምር የተፈጨ ዝንጅብልና ነጭ ሽንኩርት፣ ነጭ ቅመም፣ ትንሽ እርድ በላዩ ላይ ማድረግ አንድ የሾርባ ማንኪያ ቅቤ ጨምሮ ጨውን ማስተካከል
- ከመውጣቱ በፊት 2 ቃሪያ ሰንጠቅ አድርጎ ማውጣት :: ከዚያ ብኋላማ መረቁን ከተገኘ በእንጀራ ፈትፈት ነው ካለበለዚያም ያው በተገኘው ...
ማርታ
.
ህልበት
.
ስንቶቻችን እንሆን ህልበትን የምናውቀው? በጾም ግዜ የሚበላ ምግብ ነው።
ህልበት የሚሰራው ከባቄላ፣ ምስር እና የበቀለ አብሽ ዱቄት ነው። (ህልበት እና ስልጆ አንድ አይደሉም ይለያያሉ)
መጀመሪያ ዱቄቱ ሲዘጋጅ
3 ኬሎ ...የተከካ ባቂላ
እሩብ ከሎ በደምብ የተከካ ምስር
እሩብ ኬሎ የበቀለ አብሽ
እነዚህ ሲፈጩ የህልበት ዱቄት ይሆናሉ።
አሰራሩ
መጀመሪያ በንጹህ ድስት 2 ኩባያ ውሀ እንጥዳለን። ከዚያ ውሀው እስኪፈላልን ድረስ በንጹህ ሳህን 4 የጠረጴዛ ማንኪያ የህልበት ዱቄት በአንድ ኩባያ ቀዝቃዛ ውሀ እንበጠብጠዋለን። ...ከዚያ ውሀው ሲፈላ የበጠበጥነው ቀስ እያልን እየጨመርን ማማሰል ... ወፈር እስኪል ድረስ እናማስለዋለን። በደምብ ሲበስል ልክ እንደሽሮ ... አውርደን በሌላ እቃ ገልብጠን እናቀዘቅዘዋለን ...ከዛ ሰፋ ባለ ሳህን ላይ አድርጎ እስኪኮረፍ እና መልኩ እስኪቀየር (ነጭ ) እስኪሆን ድረስ በደምብ ይመታል። ይመታል ያኔ ለምግብነት ሲዘጋጅ በደምብ የደቀቀ ነጭ ሽንኩርት እና ቃርያ አድርገን እናዋህደዋለን
... ማርታ ...
.
ሽሮ
.
የምጣድ ሽሮ
* አንድ አነስ ያለ የፈረንጂ ሽንኩርት ወይም አንድ 4 ራስ ያበሻ ሽንኩርት ደቀቅ ብሎ ይከተፋል::
* ሁለት የሚያቃጥል ቃሪያ ደቀቅ ብሎ ይከተፋል ::
* አንድ ጭላፋ ምጥን ሽሮ
* ግማሽ ስኒ የቡና (ፍንጃል ) ዘይት አሰራሩ ሁሉንም በጎድጓዳ ሰሀን መቀላቀል እናም መበጥበጥ የንጀራ ምጣድ ማጋል ወይም እንጀራ ተጋግሮ ሲያበቃ በጋለው ላይ ያንን ማፍሰስ ቀጭን ስለሚሆን ራሱ እንደቂጣ ይዘረጋል
*መክደንና ከ5 ደቂቃ ብሁዋላ አክንባሎዉን (ሞግዱን )መክፈት
*ከዚያም በማማሰያ ወይም በማንኪያ ምጣዱ እንዳይላጥ አድርጎ ቀስ አድርጎ ባንድ ላይ ሰብስቦ ማገናበጥ ... ደረቅ ሲል ማዉጣት
* ጨው መቸም መመጠን የናንተ ፋንተ ነው እዚህ ላይ የሚጻፍ መጠን አይኖርም .. ምጥን ካልሆነ ሽሮው በርበሬ ትንሽ ጣል አድርጎ ማገናኘት መጀመሪያ ላይ አቤት ሲጣፍጥ!!
.
ቦዘና ሽሮ
* ሽንኩርት አንድ ራስ ሸርከትከት አድርጎ መክተፍ
* ከዚያም ሽንኩርቱን በዘይት ማቁላላት
* ዉሀ መጨመር በዛ አድርጎ እንደሰው ብዛት ይወሰናል ዉሀው
* ዉሀዉ ሲፈላ ሽሮዉን ነስንሶ ማማሰል ቀጠን ማለት አለበት
* በሰል ሲል ቃሪያ ሁለት ወይም ሶስት ሰንጠቅ አድሮ ጣል ማድረግና ማዉጣት።
ሽሮን እንደምታዉቁት በትኩሱ ነው :: እንጀራ ላይ አድርጎ ላፍ ላፍ ነዋ!!
ሽሮ ሳት ካልመታው ጥሩ አይደለም አንደኛ ሆድ ይነፋል ሁለተኛ ሊጥ ሊጥ ይላል ጣዕም አይኖረውም::
.
ሽሮ በቋንጣ
ያዉ አንድ ራስ ሽንኩርት መክተፍና ቋንጣዉን ቆረጥ ቆረጥ አድርጎ ሽንኩርቱን ዘይት ጨምሮ ማቁላላት .. ከዚያም ዉሀ ጨምሮ እስኪፈላ መቆየት .. ዉሀዉ ከፈላ በሁዋላ ሽሮዉን መነስነስ:: ቋንጣ ካለበት ቀይ ሽሮ ወይም ምጥን ሽሮ ቢሆን ጥሩ ነው። ሩብ ራስ ነጭ ሽንኩርትም ሊወጣ አካባቢ አስገብቶ ማብሰልና ትንሽ ቂቤ ጣል አድርጎ በትኩሱ አዉጥቶ መብላት ነው።
ማስታወሻ መልካም የሽሮ ቀን (Marta P.)
.
የቋንጣ ፍርፍር ለ3 ሰው
.
ልክ እንደማንኛውም ወጥ አሰራር በመጀምሪያ 2ራስ ቀይ ሽንኩርት ከትፈን (መድቀቅ የለበትም) ከ1ራስ ነጭ ሽንኩርት ጋር ለ3 ደቂቃ ማብሰል (ቲማቲም ከትፈን መጨምር እንቻላለን የበርበሬውን ማቃጠል ሊቀንስ ስለምችል። የቆርቆሮ ቲማቲም ከሆነ ሁለት ማንኪያ ይበቃል) ከዚያ አንድ የቡና ሲኒ የሚሆን ዘይት ጨምረን እንደገና ማብሰል። ከዚያ 2 የሾርባ ማንኪ በርበሬ (በጣም እንዲያቃጥል ካልፈለግን 1) አድርገን አሁንም በዘይቱ ከጠበስነው በሁዋላ ቋንጣውን በሌላ ምጣድ ወይንም ዝርግ መጥበሻ በደረቁ ከቆላነው በኋላ ደረቅ ሲል ቁሌቱ ዉስጥ መጨመርና ሁሉንም አብሮ አዋህዶ ለ5 ደቂቃ ማብሰል ከዚያ 1 የሾርባ ማንኪያ ቂቤ መጨመር። ቁሌቱ በደንብ ከበሰለ እና ከተዋሀደ በሁዋላ ሁለት ብርጭቆ ዉሀ በግምት አድርገን ጨው ግማሽ ማንኪያ (በምንፈልገው መጠን) አድርገን ከድኖ ማብሰል። ዉሀው ሲፈላ እና በደንብ ለ5 ደቂቃ ከተንተከተከ በሁዋላ በአገር ቤት ምጣድ 1 እንጀራ መሰባበር/መበጣጠስ እና እሳቱን በጣም እስከመጨረሻ ቀንሰን ወይም አውጥተን እንጀራውን ጨምሮ ቀስ ብሎ ቢቻል በሹካ ማገላበጥ (ካማሰልነው ሊቦካ ስለሚችል)
ከዚያ እንጀራው ከመረቁ ጋር ከተዋሀደ በዳቦ እንክት።
ድርቆሽ ከሆነ የውሀውን መጠን ጨመር ማረግ አለብን።
ማርታ ፔድሪኒ
.
የዶሮ አገነጣጠል
.
አገነጣጠሉን በአይን ካላያችሁት ለመማር ይከብዳል። ቢሆንም ያው እዚሁ ሀገር ከስፐር መርካቶ መውሰድ እንጂ ማረድ አይቻል አይደል? (ታዲያ ትንንሾቹን መግዛት ይሻላል ምክንያቱም ስጋው ወጡ ውስጥ ሲበስል ከመፈራረስ ይድናል) ትናንሾቹን ስላችሁ ደግሞ ተሳስታችሁ ወፎቻቸውን እንዳትበሉ።
1 - ክንፏ መሀል ላይ ያለውን ቆዳ እስከ ታች መቁረጥና እንዳለ ቆርጦ ማውጣት:: ከግማሽ አጥንት እስከ ትከሻዋ ያለው ይቀራል ማለት ነው ::
2 - ከአንገቷ እስከ ታች ድረስ ቆዳዋን ብቻ መሰንጠቅና ልክ ሸሚዝ እንደሚወልቅ ግፍፍ አድርጎ ማውጣት::
3 - እግርና እግሯን ወደኃላ መስበርና በቢለዋ ከላይ ከወገቧ ጀምሮ እስከ ታች መለየት ከሰውነቷ ላይ::
4 - ያንን የቀረውን ክንፍ ከትከሻ ላይ ቆርጣችሁ ከነመላላጫው ገፋችሁ ታወጡታላችሁ::
5 - በጀርባዋ በኩል ትንሽ አጥንት ከትከቻዋ የመጣና በስጋ የተሸፈነ ታገኛላችሁ ወደ ላይ በቢለዋ ታላቅቁትና በእጃችሁ ከአንገቷና ፈረሰኛውን ይዛችሁ ታላቅቁታላችሁ::
6 - አንገት፣ ጀርባ፣ የጎን አጥንት፣ ከታች በኩል ያለው የጀርባ አጥንት ይቀራል። ሁሉንም መለያየትና ጀርባውንና የጎን አጥንቱ ውስጥ ያለውን የሆድ እቃ መጣል ልቧን ማስቀረት ይቻላል (አገር ቤት ጉበቱ እሳት ውስጥ ተጠብሶ ይበላል)
7 - ፈረሰኛው ጎንና ጎኑ ላይ ስስ ከአጥንት ጋር የተያያዘውን ነገር አለ ቆርጦ ማውጣት::
8 - አንገቱን ሁለት ወይም ሦስት ቦታ መቁረጥና ወፈር ባለ ስንጥር ከመሀሉ ጨምሮ ውስጡ ያለውን ነጭ ነገር ማውጣት::
9 - እግሩ መለያያ አጥንቱ ላይ መቁረጥና (አጭሬና ረጅሜ ብሎ መለየት )
10 - ከኃላ ሆኖ ወደታች በኩል ያለው አጥንት ለሁለት ይለያል እና የመሀል ፓርቱ ይጣላል::
የረሳሁት ካለ ሙሉበት::
ማርታ
.

ቅቤ ለማንጠር
.
አራት መአዘኖቹን የዳቦ ቅቤዎች (ጨው የሌለበትን) ከሱፐርመርካቶ መግዛት። ከዛ ቅቤውን በተገኘው ቅመም (ጥቁር አዝሙድ, ኮሰረት, ኮረሪማ ... ይበቃል) መለወስና ከሁለት እስከ ሶስት ቀን ማስቀመጥ። በለስላሳ እሳት ማንጠር እና ማጥለል። የቅቤ ቅመም ከሀገር ቤት የምታስመጡ ከሆነ ግን ተቀላቅሎ የተፈጨው ጥሩ ነው። ለማንኛውም የተፈጨው ከሌላችሁ ኮረሪማውን (የተፈለፈለ) መቼም የቡናም ብረት ምጣድ ወይም ማንከሽከሻ አታጡም በሱ ትንሽ እሳት ሳታበዙ አመስ አመስ ካደረጋችሁ በኃላ አውጡትና በቡና መፍጫ በደንብ ጠራርጋችሁ ትፈጩታላችሁ። ከዛ አራት መአዘኑን የዳቦ ቅቤ ጋር ቀላቅለሽ ያው በለስላሳ እሳት ማንጠር ነው።
እዚህ የቂቤ ቅመም የት እንደሚገኝ ልጠቁማችሁ እወዳለሁ። ይህንን ማንም የሚያውቀው ሰው እንደሌለ አውቃለሁ። ህንዶች ቤት ታገኛላችሁ። ኮረሪማ፣ ጥቁር አዝሙድ፣ ... ወዘተ ... ከፈለጋችሁ። ኮሰረት ግን የሚገኝ አየመስለኝም።
ማርታ ፔድሪኒ


giovedì

70 የአለቃ ገብርሃና ቀልዶች


ከህይወት ታሪካቸው ስንጀምር አንዳንዶች የአባታቸው ስም ደስታ ተገኝ ነው ሲሉ አንዳንዶቹ ደግሞ ገብረ ማርያም ነው ይላሉ። ምናልባት አንዱ የአለም ሌላው ደግሞ የክርስትና ስማቸው ሊሆን ይችላል። የተወለዱት በደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት በድሮው የደብረታቦር አውራጃ ፎገራ ወረዳ፤ ናባጋ ጊዮርጊስ በተባለው ቦታ በ 1814 ዓ .ም ነው። የመጀመርያ ትምህርታቸውን በአካባቢው ከቀሰሙ በኃላ ወደ ጎጃም ተሻግረው ቅኔን ተቀኙ። ከዚያም ወደ ጎንደር ከተማ ተመልሰው ከመምሕር ወደ አብ ወልደ ማርያም ጽዋትወ ዜማ፤ ከባሕታዊ ገብረ አምላክ አቋቋም፤ ከዐቃቤ ስብሃት ገብረ መድሕን ትርጓሜ መጽሐፍትን እንዲሁም ድጓን ተምረዋል። በዚህ የሰፋ እውቀታቸው የተነሣ በ 26 ዓመታቸው ጎንደር ሊቀካህናትነት ተሾመው ነበር። በዚህም ሹመት ለሰባት ዓመት ማገልገላቸው ይነገራል። በፍትሐ ነገሥት ሊቅነታቸው ደግሞ በዳኝነት እየተሰየሙ አገልግለዋል። አለቃ ገብረ ሐና ጨዋታ አዋቂነታቸው እየታወቀ የመጣው በዚህ ወቅት ነበር። በዚህም እውቀታቸው የትንሹ ዓሊ አጫዋች ሆኑ። አጼ ቴዎድሮስ ሥልጣኑን ሲይዙ አለቃን በቤተ መንግሥት አገኟቸው። አለቃ የቤተ መንግሥቱን ሰዎች በቀልዳቸው ሸንቆጥ ስለሚያደርጉ መስማማት አልቻሉም ነበር። እንዲያውም ዐጼ ቴዎድሮስ «ገብረ ሐና ፍትሐ ነገስቱን ጻፍ፤ ፍርድ ስጥ .. ገንዘብ ያውልህ፤ ቀልድህን ግን ተወኝ።» ሲሉ ተናግረዋቸው ነበር ይባላል። አለቃ ግን አላቆሙም። በተለይም ደግሞ በንጉሡ ባለሟል በብላታ አድጎ ላይ «አድግ / በግእዝ አህያ ማለት ነው /» እያሉ በሚሰነዝሩት ትችት በተደጋጋሚ ተከሰው ዐጼ ቴዎድሮስ ዘንድ ቀርበዋል። በመጨረሻ ቴዎድሮስ ክስ ሲሰለቻቸው ምላስ ቀርቶ ታገሉና ተሸናነፉ ብለው ፈረዱ። በዚህም ትግል ምሁሩ አለቃ ተሸነፉ። ንጉሡም እንግዲህ ምን ይበጅህ ? ሲሉ ጠየቋቸው አለቃም «ድሮስ ትግል የአህያ ሥራ አይደል» ብለው በመመለሣቸው ከአካባቢያቸው ለማራቅ ሲሉ ንጉሡ ገብረ ሐናን ለትግራይ ጨለቆት ሥላሴ አለቃ አድርገው በመሾም ወደ ትግራይ ላኳቸው። ወደካቶሊክነት የተቀየረውና ከአንቷን ዳባዲ ጋር በዐጼ ቴዎድሮስ ዘመን ስለሆነው ሁሉ ደብዳቤ ይለዋወጥ የነበረው የዋድላው ሰው ደብተራ አሰጋኽኝ ጥር 1858 ዓ .ም . ለአንቷን ዳባዲ በጻፈው ደብዳቤ እንዲህ በማለት ይህን ሁኔታ ገልጦት ነበር «አለቃ ገብረ ሐናን ንጉሥ መቱዋቸው። ወደ ትግሬ ወደ ላስታ ተሰደዱ። እጅግ ተዋረዱ እኔም በዋድላ አገኘኋቸው ወደ ቆራጣም ሄዱ» ሲል ጽፏል። ደስታ እንዳለ ሁሉ መከራም ያለ ስለሆነ ሁለቱንም በጸጋ መቀበል የሰው ልጅ ሁሉ ግዴታ ነው። ካህናት በአጼ ቴዎድሮስ ላይ ባመጹ ጊዜ በአድማው ካሉበት ካህናት መካከል አንዱ ገብረ ሐና መሆናቸው ስለታወቀ ዐጼ ቴዎድሮስ በአለቃ ገብረ ሐና ላይ አምርረው ሊቀጧቸው ዛቱ። አለቃም ሸሽተው ጣና ሐይቅ ሬማ መድኃኔዓለም ገዳም ገቡ። በዚያም ባሕታዊ ጸዐዳ ገብረ ሥላሴ የተባሉ የአቋቋም ሊቅ አገኙ። ሁለቱም ተወያይተው በጎንደር አቋቋም ስልት የመቋሚያውን የአካል እንቅስቃሴ ጨምረው ዝማሜውን አዘጋጁት (በኋላ ተክሌ አቋቋም እየተባለ የሚታወቀው ነው )። ባህታዊ ጸዐዳ «ከእንግዲህ እኔ ወደ ዓለም አልመለስም፤ አንተ ይህንን ስልት አስተምር» ብለው አለቃ ገብረሐናን አደራ አሏቸው። ከዐጼ ቴዎድሮስ ሞት በዃላ በ 1864 ዓ .ም . ዐጼ ዮሐንስ ሲነግሡ ከገዳም ወጥተው ወደ ትግራይ አቀኑ። በመቀጠልም በቴዎድሮስ ቤተመንግሥት ሳሉ የሚያውቋቸው ምኒልክ በሸዋ መንገሣቸውን ተከትለው ሸዋ መጡ። ዐጼ ምኒልክ በዐጼ ቴዎድሮስ ቤተመንግሥት ሳሉ አለቃ ገብረ ሐናን ስለሚያውቋቸው በደቡብ ጎንደር የሚገኘውን የአቡነ ሐራን ገዳም ሾሟቸው። በዚያም ጊዜ በአካባቢው ከባድ ርሃብ በመከሠቱ አለቃ ከገዳሙ ብር አንድ ሺ አውጥተው ለገበሬዎች አከፋፈሏቸው። በዚህም ተግባራቸው ተከስሰው ወደ አዲስ አበባ መጡ። የፍርድ ሚኒስቴር የነበሩት አፈ ንጉሥ ነሲቡ ስሕተት ነው ብለው ፈርደውባቸው ነበር። ነገር ግን ጉዳዩ በምኒልክ ዘንድ ስለተሰማ ወደ ዙፋኑ ችሎት ተሻገረ። ዐጼ ምኒልክም ይህ ተግባር ያሸልማል እንጂ አያስቀጣም ብለው በመፍረዳቸው አለቃ ነጻ ወጡ። ንጉሥ ምኒልክ አለቃን የእንጦጦ ራጉኤል አለቃ አድርገው ሾሟቸው። እርሳቸውም ትርጓሜ መጻሕፍትን ያስተምሩ ነበር። ጥቂት ጊዜ በአዲስ አበባ እንደ ተቀመጡ እንደገና ወደ ጎንደር ተመልሰው፤ ድንግልናቸውን አፍርሰው ወይዘሮ ማዘንጊያን አገቡና ተክሌ የተባለ አንድ ወንድ ልጅና በፍታ የተባለች ሴት ልጅ ወለዱ። አንዳንድ ሊቃውንት አለቃ ገብረ ሐና ሊቅ፤ መልከመልካምና የነገሥታቱ ወዳጅ በመሆናቸው በዚያ ዘመን የነበሩ ሴቶች ወዳጅነት ለማበጀት ይሻሙባቸው ነበር ይላሉ። አለቃ ድንግልናቸውን ያፈረሱት ሆን ብለው ሳይሆን እኔ አስፈርሰዋለሁ በሚል የወይዛዝርት ውድድር የተነሣ ነው ይባላል። የአለቃ መንፈሳዊ ሕይወት የተናጋው ከዚያ በዃላ ነው ይባላል። ተክሌ ለትምህርት ሲደርስ ከሌላው የቤተክርስቲያን ትምህርት ጋር እርሳቸው ከባሕታዊ ጸዐዳ ገብረ ሥላሴ ጋር ሆነው ያዘጋጁትን ዝማሜ አስተማሩት። አለቃ ገብረ ሐና ደርቡሽ ጎንደርን ሲወርር ልጃቸውን ወደ ወሎ ልከው እርሳቸው ጎጃም ውስጥ ዘጌ ገዳም ገቡ። በዃላም ዐጼ ምኒልክ ደርቡሽን ለመውጋት ወደ ፎገራ መምጣታቸውን ሲሰሙ፤ ከተደበቁበት ወጥተው ንጉሡን ተከትለው ወደ አዲስ አበባ ተመለሱ። ምኒልክም እንደገና የራጉኤል አለቃ አድርገው ሾሟቸው። ልጃቸው አለቃ ተክሌ ወሎ ንጉሥ ሚካኤል ዘንድ እያሉ የተንታ ሚካኤል በዓል ሲከበር ከአባታቸው የተማሩትን ዝማሜ በተመስጦ አቀረቡት። ንጉሥ ሚካኤልም በዚህ ተደንቀው በዚያው በተንታ እንዲያገለግሉ አደረጉ። የተክሌ ዝማሜ በይፋ የተጀመረው ያኔ ነው ይባላል። በዃላ ራስ ጉግሣ የአለቃ ተክሌን ዝና ሰምተው ንጉሥ ሚካኤልን በማስፈቀድ ወደ ደብረ ታቦር አምጥተው የኢየሱስ ቤተክርስቲያን ሾሟቸው። አለቃ በአዲስ አበባ እያሉ ከመኳንንቱ ከመሳፍንቱ ጋር ያላስማሟቸው ብዙ ነገሮች ነበሩ። የመጀመርያው ትንባሆ ይጠጣሉ ተብሎ የተነገረው ሐሜት አንድ ቀን በቅኔ ማኅሌት ፒፓቸው ወድቆ በመጋለጣቸው ነው። ከዚህም በተጨማሪ በአድዋ ጦርነት ታላቅ ጀብዱ ለፈጸሙት ለደጃዝማች ባልቻ ዐጼ ምኒልክ የሚወዷትን ጎራዴያቸውን ሲሸልሟቸው «ወይ ጎራዴ ወይ ጎራዴ ከቤቷ ገባች» በማለት በሽሙጥ በመናገራቸው ባልቻ እገላለሁ ብለው ተነሡ። ይህም አልበቃ ብሏቸው ከእቴጌ ጣይቱ ጋር በነገር ተኳረፉና መላ የቤተመንግሥቱ ሰው አደመባቸው። ዐጼ ምኒልክ አለቃን ምን ቢወዷቸው በተለይ ከደጃች ባልቻና እቴጌ ጣይቱ ጋር የፈጠሩትን ጠብ አልወደዱላቸውም። በዚህ ምክንያት አለቃ ገብረ ሐና ከአዲስ አበባ ለቅቀው እንዲወጡ ተወሰነባቸው። በጎንደርና በወሎ ጥቂት ጊዜ ከሰነበቱ በዃላ ልጃቸውን ገብረ ሐና ሞተ ብለህ ተናገር ብለው አዲስ አበባ ላኩት። አለቃ ተክሌ ይህንን መርዶ በቤተመንግሥቱ ሲያረዱ ምንም እንኳ ገብረ ሐና ከብዙዎቹ ጋር ቢኳረፉም ታላቅ ሐዘን ሆነ። ከተወሰኑ ቀናት በዃላ አለቃ ራሳቸው አዲስ አበባ ገቡና ጉድ አሰኙ። ምኒልክም አስጠርተው ሞቱ ከተባለው በዃላ ከየት መጡ ቢባሉ «በሰማይ ጣይቱ የለች፤ ምኒልክ የለ፤ ጠጅ የለ፤ ጮማ የለ፤ ባዶ ቤት ቢሆንብኝ ለጠባቂው ጉቦ ሰጥቼ መጣሁ።» ብለው ሁሉንም አሳቋቸው። ጣይቱም መኳንንቱም ይቅር አሏቸው። አለቃ ገብረ ሐና እድሜያቸው እየገፋ አደብም እየገዙ መጡ አዲስ አበባ ተቀምጠውም ትርጓሜ መጽሐፍት ማስተማር ቀጠሉ። ዐጼ ምኒልክ የአብያተ ክርስቲያናቱን የግብዝና መሬት ለመኳንንቱ በመስጠታቸው ካህናቱ ምንም ባለ ማግኘታቸው የተቆጡት አለቃ ገብረ ሐና ተቃውሟቸውን በቀልድ ለዐጼ ምኒልክ አቀረቡ። ይህም ከወይዛዝርቱና ከመኳንንቱ ጋር መልሶ አጋጫቸው። ከዚህ በዃላ አዲስ አበባ መቀመጥ ስላልቻሉ ለመጨረሻ ጊዜ ወደ ደብረ ታቦር ተመለሱ። ያኔ ልጃቸው አለቃ ተክሌ ደብረ ታቦር ኢየሱስን እልቅና ተሾመው ነበር። ለጥቂት ቀናት ደብረ ታቦር ከልጃቸው ጋር ሰንብተው ወደ ትውልድ ቦታቸው ናባጋ ጊዮርጊስ መጡ። በእድሜያቸው መጨረሻ ዝምተኛ ሆነው ነበር ቀድሞ በሠሩት ሥራ እየተጸጸቱ አንደበታቸውን ከነገር ዘርቅ ከለከሉ። ከጥሩ ምግብና ከጥሩ መጠጥ ተቆጠቡ። ቅዱሳን መጻሕፍትን ሰብስበው «መሳቂያና መሳለቂያ አደረግዃችሁ» እያሉ ይቅርታ ይጠይቁ ነበር ይባላል። በዚህ ሁኔታ ከሰነበቱ በዃላ በ 84 ዓመታቸው የካቲት 1898 ዓ .ም . ዐረፉ። አለቃ ገብረ ሐና ብብዙ ሰዎች ዘንድ በቀልደኝነታቸው ይታወቁ እንጂ በቤተክርስቲያን ታሪክ ወደር ከማይገኝላቸው ሊቃውንት አንዱ ነበሩ። አለቃ ለማ ኃይሉ (የደራሲ መንግስቱ ለማ አባት ) ሰለ አለቃ ገብረ ሃና ሊቅነት ሲናገሩ « የሞያ መጨረሻ እርሳቸው አይደሉም ወይ ? የሐዲስ መምህር ናቸው። የፍትሐ ነገስት መምህር ናቸው። መርሐ እውሩን፤ አቡሻሩን የሚያውቁ ባለሙያ ናቸው። ለዚህ ለዝማሜ እሚባለው ለመቋሚያ እገሌ ይመስለዋል አይባልም። ከገብረ ሐና ፊት የሚዘም የለም።» ብለዋል። ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴም «አለቃ ገብረ ሐና እጅግ የተማሩ የጎንደር ሊቅ ነበሩ። በዚህም በላይ ኃይለ ቃልና ጨዋታ ያውቁ ነበር» በማለት ይገልጿቸዋል። (ምንጭ (ዚና ሰኔ 1999)) ።በ 1998 ዚና እንዳጻፈው ደግሞ አለቃ ገብረ ሃና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሊቅ ሲሆኑ አቋቋምና ዜማ ቅኔ ከእነ አግባቡ የሚያውቁ እንደነበሩ ታሪካቸው ያስረዳል። አለቃ ባልሳሳት የነበሩበት በአጼ ምንይልክ ዘመን ይመስለኛል። በቅርቡ የሳቸውንና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ሊቃውንት ታሪክ የያዘ መጽሐፍ የታተመ ስለኆነ ስለሳቸውም ኆነ ስለሌሎች ባለ ታሪኮች ጥሩ ግንዛቤ ይኖረናል እላለሁ። አሳታሚው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ ሲኆን በቅርቡ በገበያ ላይ እንደ ሚውል ተስፋ አለኝ።

/////////////////////////////////////////////


አለቃ ገብረ ሐና
ከWikipedia
ከህይወት ታሪካቸው ስንጀምር አንዳንዶች የአባታቸው ስም ደስታ ተገኝ ነው ሲሉ አንዳንዶቹ ደግሞ ገብረ ማርያም ነው ይላሉ። ምናልባት አንዱ የአለም ሌላው ደግሞ የክርስትና ስማቸው ሊሆን ይችላል። የተወለዱት በደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት በድሮው የደብረታቦር አውራጃ ፎገራ ወረዳ፤ ናብጋ ጊዮርጊስ በተባለው ቦታ በ1814 ዓ.ም ነው። የመጀመርያ ትምህርታቸውን በአካባቢው ከቀሰሙ በኃላ ወደ ጎጃም ተሻግረው ቅኔን ተቀኙ። ከዚያም ወደ ጎንደር ከተማ ተመልሰው ከመምሕር ወደ አብ ወልደ ማርያም ጽዋትወ ዜማ፤ ከባሕታዊ ገብረ አምላክ አቋቋም፤ ከዐቃቤ ስብሃት ገብረ መድሕን ትርጓሜ መጽሐፍትን እንዲሁም ድጓን ተምረዋል። በዚህ የሰፋ እውቀታቸው የተነሣ በ26 ዓመታቸው ጎንደር ሊቀካህናትነት ተሾመው ነበር። በዚህም ሹመት ለሰባት ዓመት ማገልገላቸው ይነገራል። በፍትሐ ነገሥት ሊቅነታቸው ደግሞ በዳኝነት እየተሰየሙ አገልግለዋል። አለቃ ገብረ ሐና ጨዋታ አዋቂነታቸው እየታወቀ የመጣው በዚህ ወቅት ነበር። በዚህም እውቀታቸው የትንሹ ዓሊ አጫዋች ሆኑ። አጼ ቴዎድሮስ ሥልጣኑን ሲይዙ አለቃን በቤተ መንግሥት አገኟቸው። አለቃ የቤተ መንግሥቱን ሰዎች በቀልዳቸው ሸንቆጥ ስለሚያደርጉ መስማማት አልቻሉም ነበር። እንዲያውም ዐጼ ቴዎድሮስ «ገብረ ሐና ፍትሐ ነገስቱን ጻፍ፤ ፍርድ ስጥ .. ገንዘብ ያውልህ፤ ቀልድህን ግን ተወኝ።» ሲሉ ተናግረዋቸው ነበር ይባላል። አለቃ ግን አላቆሙም።
በተለይም ደግሞ በንጉሡ ባለሟል በብላታ አድጎ ላይ «አድግ / በግእዝ አህያ ማለት ነው /» እያሉ በሚሰነዝሩት ትችት በተደጋጋሚ ተከሰው ዐጼ ቴዎድሮስ ዘንድ ቀርበዋል። በመጨረሻ ቴዎድሮስ ክስ ሲሰለቻቸው ምላስ ቀርቶ ታገሉና ተሸናነፉ ብለው ፈረዱ። በዚህም ትግል ምሁሩ አለቃ ተሸነፉ። ንጉሡም እንግዲህ ምን ይበጅህ? ሲሉ ጠየቋቸው አለቃም «ድሮስ ትግል የአህያ ሥራ አይደል» ብለው በመመለሣቸው ከአካባቢያቸው ለማራቅ ሲሉ ንጉሡ ገብረ ሐናን ለትግራይ ጨለቆት ሥላሴ አለቃ አድርገው በመሾም ወደ ትግራይ ላኳቸው። ወደካቶሊክነት የተቀየረውና ከአንቷን ዳባዲ ጋር በዐጼ ቴዎድሮስ ዘመን ስለሆነው ሁሉ ደብዳቤ ይለዋወጥ የነበረው የዋድላው ሰው ደብተራ አሰጋኽኝ ጥር 1858 ዓ.ም. ለአንቷን ዳባዲ በጻፈው ደብዳቤ እንዲህ በማለት ይህን ሁኔታ ገልጦት ነበር «አለቃ ገብረ ሐናን ንጉሥ መቱዋቸው። ወደ ትግሬ ወደ ላስታ ተሰደዱ። እጅግ ተዋረዱ እኔም በዋድላ አገኘኋቸው ወደ ቆራጣም ሄዱ» ሲል ጽፏል።
ደስታ እንዳለ ሁሉ መከራም ያለ ስለሆነ ሁለቱንም በጸጋ መቀበል የሰው ልጅ ሁሉ ግዴታ ነው። ካህናት በአጼ ቴዎድሮስ ላይ ባመጹ ጊዜ በአድማው ካሉበት ካህናት መካከል አንዱ ገብረ ሐና መሆናቸው ስለታወቀ ዐጼ ቴዎድሮስ በአለቃ ገብረ ሐና ላይ አምርረው ሊቀጧቸው ዛቱ። አለቃም ሸሽተው ጣና ሐይቅ ሬማ መድኃኔዓለም ገዳም ገቡ። በዚያም ባሕታዊ ጸዐዳ ገብረ ሥላሴ የተባሉ የአቋቋም ሊቅ አገኙ። ሁለቱም ተወያይተው በጎንደር አቋቋም ስልት የመቋሚያውን የአካል እንቅስቃሴ ጨምረው ዝማሜውን አዘጋጁት (በኋላ ተክሌ አቋቋም እየተባለ የሚታወቀው ነው)። ባህታዊ ጸዐዳ «ከእንግዲህ እኔ ወደ ዓለም አልመለስም፤ አንተ ይህንን ስልት አስተምር» ብለው አለቃ ገብረሐናን አደራ አሏቸው። ከዐጼ ቴዎድሮስ ሞት በዃላ በ1864 ዓ.ም. ዐጼ ዮሐንስ ሲነግሡ ከገዳም ወጥተው ወደ ትግራይ አቀኑ። በመቀጠልም በቴዎድሮስ ቤተመንግሥት ሳሉ የሚያውቋቸው ምኒልክ በሸዋ መንገሣቸውን ተከትለው ሸዋ መጡ።
ዐጼ ምኒልክ በዐጼ ቴዎድሮስ ቤተመንግሥት ሳሉ አለቃ ገብረ ሐናን ስለሚያውቋቸው በደቡብ ጎንደር የሚገኘውን የአቡነ ሐራን ገዳም ሾሟቸው። በዚያም ጊዜ በአካባቢው ከባድ ርሃብ በመከሠቱ አለቃ ከገዳሙ ብር አንድ ሺ አውጥተው ለገበሬዎች አከፋፈሏቸው። በዚህም ተግባራቸው ተከስሰው ወደ አዲስ አበባ መጡ። የፍርድ ሚኒስቴር የነበሩት አፈ ንጉሥ ነሲቡ ስሕተት ነው ብለው ፈርደውባቸው ነበር። ነገር ግን ጉዳዩ በምኒልክ ዘንድ ስለተሰማ ወደ ዙፋኑ ችሎት ተሻገረ። ዐጼ ምኒልክም ይህ ተግባር ያሸልማል እንጂ አያስቀጣም ብለው በመፍረዳቸው አለቃ ነጻ ወጡ። ንጉሥ ምኒልክ አለቃን የእንጦጦ ራጉኤል አለቃ አድርገው ሾሟቸው። እርሳቸውም ትርጓሜ መጻሕፍትን ያስተምሩ ነበር። ጥቂት ጊዜ በአዲስ አበባ እንደ ተቀመጡ እንደገና ወደ ጎንደር ተመልሰው፤ ድንግልናቸውን አፍርሰው ወይዘሮ ማዘንጊያን አገቡና ተክሌ የተባለ አንድ ወንድ ልጅና በፍታ የተባለች ሴት ልጅ ወለዱ። አንዳንድ ሊቃውንት አለቃ ገብረ ሐና ሊቅ፤ መልከመልካምና የነገሥታቱ ወዳጅ በመሆናቸው በዚያ ዘመን የነበሩ ሴቶች ወዳጅነት ለማበጀት ይሻሙባቸው ነበር ይላሉ። አለቃ ድንግልናቸውን ያፈረሱት ሆን ብለው ሳይሆን እኔ አስፈርሰዋለሁ በሚል የወይዛዝርት ውድድር የተነሣ ነው ይባላል። የአለቃ መንፈሳዊ ሕይወት የተናጋው ከዚያ በዃላ ነው ይባላል። ተክሌ ለትምህርት ሲደርስ ከሌላው የቤተክርስቲያን ትምህርት ጋር እርሳቸው ከባሕታዊ ጸዐዳ ገብረ ሥላሴ ጋር ሆነው ያዘጋጁትን ዝማሜ አስተማሩት። አለቃ ገብረ ሐና ደርቡሽ ጎንደርን ሲወርር ልጃቸውን ወደ ወሎ ልከው እርሳቸው ጎጃም ውስጥ ዘጌ ገዳም ገቡ። በዃላም ዐጼ ምኒልክ ደርቡሽን ለመውጋት ወደ ፎገራ መምጣታቸውን ሲሰሙ፤ ከተደበቁበት ወጥተው ንጉሡን ተከትለው ወደ አዲስ አበባ ተመለሱ። ምኒልክም እንደገና የራጉኤል አለቃ አድርገው ሾሟቸው። ልጃቸው አለቃ ተክሌ ወሎ ንጉሥ ሚካኤል ዘንድ እያሉ የተንታ ሚካኤል በዓል ሲከበር ከአባታቸው የተማሩትን ዝማሜ በተመስጦ አቀረቡት። ንጉሥ ሚካኤልም በዚህ ተደንቀው በዚያው በተንታ እንዲያገለግሉ አደረጉ። የተክሌ ዝማሜ በይፋ የተጀመረው ያኔ ነው ይባላል። በዃላ ራስ ጉግሣ የአለቃ ተክሌን ዝና ሰምተው ንጉሥ ሚካኤልን በማስፈቀድ ወደ ደብረ ታቦር አምጥተው የኢየሱስ ቤተክርስቲያን ሾሟቸው። አለቃ በአዲስ አበባ እያሉ ከመኳንንቱ ከመሳፍንቱ ጋር ያላስማሟቸው ብዙ ነገሮች ነበሩ። የመጀመርያው ትንባሆ ይጠጣሉ ተብሎ የተነገረው ሐሜት አንድ ቀን በቅኔ ማኅሌት ፒፓቸው ወድቆ በመጋለጣቸው ነው። ከዚህም በተጨማሪ በአድዋ ጦርነት ታላቅ ጀብዱ ለፈጸሙት ለደጃዝማች ባልቻ ዐጼ ምኒልክ የሚወዷትን ጎራዴያቸውን ሲሸልሟቸው «ወይ ጎራዴ ወይ ጎራዴ ከቤቷ ገባች» በማለት በሽሙጥ በመናገራቸው ባልቻ እገላለሁ ብለው ተነሡ። ይህም አልበቃ ብሏቸው ከእቴጌ ጣይቱ ጋር በነገር ተኳረፉና መላ የቤተመንግሥቱ ሰው አደመባቸው። ዐጼ ምኒልክ አለቃን ምን ቢወዷቸው በተለይ ከደጃች ባልቻና እቴጌ ጣይቱ ጋር የፈጠሩትን ጠብ አልወደዱላቸውም። በዚህ ምክንያት አለቃ ገብረ ሐና ከአዲስ አበባ ለቅቀው እንዲወጡ ተወሰነባቸው። በጎንደርና በወሎ ጥቂት ጊዜ ከሰነበቱ በዃላ ልጃቸውን ገብረ ሐና ሞተ ብለህ ተናገር ብለው አዲስ አበባ ላኩት። አለቃ ተክሌ ይህንን መርዶ በቤተመንግሥቱ ሲያረዱ ምንም እንኳ ገብረ ሐና ከብዙዎቹ ጋር ቢኳረፉም ታላቅ ሐዘን ሆነ። ከተወሰኑ ቀናት በዃላ አለቃ ራሳቸው አዲስ አበባ ገቡና ጉድ አሰኙ። ምኒልክም አስጠርተው ሞቱ ከተባለው በዃላ ከየት መጡ ቢባሉ «በሰማይ ጣይቱ የለች፤ ምኒልክ የለ፤ ጠጅ የለ፤ ጮማ የለ፤ ባዶ ቤት ቢሆንብኝ ለጠባቂው ጉቦ ሰጥቼ መጣሁ።» ብለው ሁሉንም አሳቋቸው። ጣይቱም መኳንንቱም ይቅር አሏቸው። አለቃ ገብረ ሐና እድሜያቸው እየገፋ አደብም እየገዙ መጡ አዲስ አበባ ተቀምጠውም ትርጓሜ መጽሐፍት ማስተማር ቀጠሉ። ዐጼ ምኒልክ የአብያተ ክርስቲያናቱን የግብዝና መሬት ለመኳንንቱ በመስጠታቸው ካህናቱ ምንም ባለ ማግኘታቸው የተቆጡት አለቃ ገብረ ሐና ተቃውሟቸውን በቀልድ ለዐጼ ምኒልክ አቀረቡ። ይህም ከወይዛዝርቱና ከመኳንንቱ ጋር መልሶ አጋጫቸው። ከዚህ በዃላ አዲስ አበባ መቀመጥ ስላልቻሉ ለመጨረሻ ጊዜ ወደ ደብረ ታቦር ተመለሱ። ያኔ ልጃቸው አለቃ ተክሌ ደብረ ታቦር ኢየሱስን እልቅና ተሾመው ነበር። ለጥቂት ቀናት ደብረ ታቦር ከልጃቸው ጋር ሰንብተው ወደ ትውልድ ቦታቸው ናባጋ ጊዮርጊስ መጡ። በእድሜያቸው መጨረሻ ዝምተኛ ሆነው ነበር ቀድሞ በሠሩት ሥራ እየተጸጸቱ አንደበታቸውን ከነገር ዘርቅ ከለከሉ። ከጥሩ ምግብና ከጥሩ መጠጥ ተቆጠቡ። ቅዱሳን መጻሕፍትን ሰብስበው «መሳቂያና መሳለቂያ አደረግዃችሁ» እያሉ ይቅርታ ይጠይቁ ነበር ይባላል። በዚህ ሁኔታ ከሰነበቱ በዃላ በ84 ዓመታቸው የካቲት 1898 ዓ.ም. ዐረፉ። አለቃ ገብረ ሐና በብዙ ሰዎች ዘንድ በቀልደኝነታቸው ይታወቁ እንጂ በቤተክርስቲያን ታሪክ ወደር ከማይገኝላቸው ሊቃውንት አንዱ ነበሩ። አለቃ ለማ ኃይሉ (የደራሲ መንግስቱ ለማ አባት) ሰለ አለቃ ገብረ ሃና ሊቅነት ሲናገሩ « የሞያ መጨረሻ እርሳቸው አይደሉም ወይ ? የሐዲስ መምህር ናቸው። የፍትሐ ነገስት መምህር ናቸው። መርሐ እውሩን፤ አቡሻሩን የሚያውቁ ባለሙያ ናቸው። ለዚህ ለዝማሜ እሚባለው ለመቋሚያ እገሌ ይመስለዋል አይባልም። ከገብረ ሐና ፊት የሚዘም የለም።» ብለዋል። ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴም «አለቃ ገብረ ሐና እጅግ የተማሩ የጎንደር ሊቅ ነበሩ። በዚህም በላይ ኃይለ ቃልና ጨዋታ ያውቁ ነበር» በማለት ይገልጿቸዋል። (ምንጭ (ዚና ሰኔ 1999)) ።በ1998 ዚና እንዳጻፈው ደግሞ አለቃ ገብረ ሃና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሊቅ ሲሆኑ አቋቋምና ዜማ ቅኔ ከእነ አግባቡ የሚያውቁ እንደነበሩ ታሪካቸው ያስረዳል። አለቃ ባልሳሳት የነበሩበት በአጼ ምንይልክ ዘመን ይመስለኛል። በቅርቡ የሳቸውንና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ሊቃውንት ታሪክ የያዘ መጽሐፍ የታተመ ስለኆነ ስለሳቸውም ኆነ ስለሌሎች ባለ ታሪኮች ጥሩ ግንዛቤ ይኖረናል እላለሁ። አሳታሚው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ (ዳንኤል አበራ፣ 2000 ዓ.ም.)

/////////////////////////////////////////////

1 እሳት የማያጠፋው ውሀ፡
2 ቀበጡዋ እመቤት
3 ሁለቱ እብዶች
4 የእብድ አናጺ
5 ስጋ ሻጭ ና አብዱ
6 ጎጃምን ምታ ጎንደርን ምታ
7 'አለቃ ገብረ ሐና እና ቀልዶቻቸው' ተዘጋጀ በዳንኤል አበራ 2000 አ.ም.
8 ሃድጎ -አህያ ሸራህያ
9 ጎመን እያበሰልሁ ነው
10 አይ ጎራዴ አይ አስተጣጠቅ
11 እንደምን አደራችሁ
12 እሱን ይጨርሱና
13 አሸነፈቻቸው
14 ሌላ እደግሞታለሁ
15 እያሳራኝ ነው
16 አለቃ ገብረ ሃና ሞቱ
17 አሬን ስበላ ከረምሁ (1)
18 አሬን ስበላ ከረምሁ (2)
19 አምባው ተሰበረ
20 አለመመጣጠን
21 አለቃ ወረኃና በጣም አጭር - ድንክዬ ሰው ናቸው
22 ገብተሽ አልቀሽ
23 ለሰማይ የምትቀርቢ
24 እዚያም ቤት እሳት አለ
25 በጃቸው
26 ደርቆ ተንጣጣ
27 እሷ ትታቀፋለች
28 ውዳሴ ማርያም ልደገም
29 ቁጭ ብዬ ሳመሽ
30 ጉድ ባይ ብዬ መጣሁ
31 አስበጂና ላኪልኝ
32 ማን ደፍሮ ይገባል
33 ምልምሎች
34 ጭን እያነሱ መስጠት
35 ዋናውን ይዘው
36 እኔ ለነካሁት
37 መውጫችንን ነዋ
38 ኩኩሉ
39 በጠማማ ጣሳ
40 አስደግፈውት አመለጡ
41 በሰው አገር ቀረሁ
42 ከአልጋ ላይ ወድቄ ነው
43 የተልባ ማሻው ሚካኤል
44 ወላሂ ኑ እንብላ
45 ግም ግም ሲል
46 ቢሻን እንበላለን ቢሻን እንጠጣለን
47 ከመሶብዎ አይጡ
48 የመጣሁበት ነው
49 ጠረር አርገሽ ቅጂው
50 ዝግንትሉ ሞልቷል
51 ጥፍር ያስቆረጥማል
52 የጓደኛህን ቀን ይስጥህ
53 በቁሜ ቀምሼ መጣሁ
54 ሺ ነዋ
55 ቡሊ የአለቃ አህያ
56 በጠማማ ቁና ሁለት ሁለት (1)
57 በጠማማ ቁና ሶስት ሶስት (2)
58 አለቃ አለ ዕቃ
59 ሰይጣኑ ይውለድህ
60 በሌባ ጣትሽ አታሳዪኝ
61 አንቺ ባይበላሽ (1)
62 አንቺ ባይበላሽ (2)
63 ቤቴ በየት ዞረህ መጣህ
64 መቋሚያዬን አቀብዪኝ
65 ባዶ ሽሮ
66 ነዪ ብዪ እንጂ
67 ገብርኤልና ሚካኤል ተታኮሱ
68 ለምን ደወልሽው
69 ቃታ መፈልቀቂያሽን
70 ጠረር አድርገሽ ቅጂው
71 አንድማ ግዙ
72 በጠርር ሄጄ በታህሳሥሥ
73 መልግጌ አባስኩት
74 ድንቼ
75 በነካ አፍህ
76 ተኖረና ተሞተ
77 መሞትዎት ነው
78 የአለቃ የልጅ ልጅ



እሳት የማያጠፋው ውሀ፡
ሰውየው ዳብዳቤ በመጻፍ ላይ ሳለ፡ ሠራተኛው በሩን በርግዳ ትገባና "ጌታዬ፡ ማድቤቱ በእሳት ተያይዟል" ትለዋልች። ባለቤትየው ገስግሶ እማድቤቱ ሲደርስም መለስተኛ እሳትና ምድጃው ላይ ተጥዶ የሚንከተከተውን ድስት ሙሉ ውሃ ያያል። በዚህ ጊዜ ተናዶ "አንች ደደብ፡ ወደኔ ከመምጣት ይልቅ የሚፍለቀለቀውን ውሃ አታፈሽበትም ኖሯል?" በማለት ቢገስጻት "ጌታዬ ውሃው'ኮ የፈላ ስለሆነ አያጠፋውም ብዬ ነው" ብላ አሳቀችው።


ቀበጡዋ እመቤት
እመቤቲቱ የባለቤታቸው ጦር ሜዳ መቆየት አላስችል ይላቸውና ከአንዱ ባሪያቸው ጋር የቀበጣሉ። እንዳየደርስ የለም ባል ሳይጠበቁ ከች ይላሉ። ሚስጥራቸው እንዳይወጣ ያሰቡት ሚስትም ስራተኛቸውን ባፋጣኝ ወደባሪያቸው እንዲህ ብለው ይልካሉ 'ባለፈው የተፈጠረውን ነገር ለማነም እንዳትናገር'። ሰራተኛየቱም ብዙ ስዎች ይሰሩበት ወደነበር እርሻ ሄዳ አፋፉ ላይ ትቆምና ስሙን ጠርታ 'እመቤቴ የባለፈውን ነገር ለማንም እንዳትናገር ብለውሃል'ትለዋለች። እሱም መለስ ያደርግና 'ምንም ችግር የለም እኔ ምኔ ሞኝ ነው እመቤቴን በ*ሁ ብዬ የማወራው' ብሎዋት እርፍ። ተፈጸመ


ሁለቱ እብዶች
ሁለት እብዶች ከአማኑኤል ሆስፒታል ዘበኛውን አታልለው ለማምለጥ ይመካከራሉ። በምክራቸው መሰረት ወደመግቢያው ሲያመሩ ዘበኛው በአካባቢው የለም። በመጥፋት ፋንታ እቅዳቸው እንደተበላሸ በማሰብ ወደነበሩበት ተመለሱ።


የእብድ አናጺ
አማኑኤል ሆስፒታል ውስጥ አንዱ እብድ ፎቶ ግድግዳ ላይ ለመስቀል ፈልጎ ሚስማሩን ገልብጦ በመዶሻ ግድግዳው ላይ ለመምታት ይታገላል:: አንድ ሌላ እብድ ባጠገቡ ሲያልፍ ያየውና በሳቅ ይሞታል:: ይሄኛው እብድ ምን ያስቅሃል ይለዋል; እሱም ዝም ብለህ ትለፋለህ የያዝከው ሚስማር እኮ የተሰራው ለዛኛው ግድግዳ ነው ብሎ የሚስማሩ ጫፍ ውደሚያሳይበት ግድግዳ አሳየው::


ስጋ ሻጭ ና አብዱ
አንድ አብድ በስጋ መሽጫ ሱቅ በር ላይ ቆም ሲል ያየ ስጋ ሻጭ በጭራው ሊያስፈራራው አየሞከረ ፤ አትሄድም ከዚህ አንተ አብድ ፡ብሎ ይጮህበታል አብዱም ሳቅ ብሎ <የሞተ ፣አሬሳ ስቅለህ ዝንቡን አሽ ፣አሽ ስትል የምትውል አብድስ አንተ ...> ብሎት አርፍ


ጎጃምን ምታ ጎንደርን ምታ
አንድ በጣም ወፍራም ሴትዮ የእንጦጦን ጋራ በእግራቸው ለመውጣት ይያያዙታል ። ሲደክማቸው ኋላቸውን ዞር በማለት እየተመለከቱ በማረፍ ሲጓዙ አንዴ ፈሳቸውን ብው ሲያደርጉ «ጎጃምን ምታ !» ይላሉ ። አሁንም ወጥተው ወጥተው ሲደክማቸው ዞር ብለው በማየት ፈሳቸውን « ብም ..ብም ..ቡዋ !» ሲያደርጉት «ጎንደርን ምታ !» ይላሉ። በመጨረሻም ዞር ዞር ብለው በመመልከት ፈሳቸውን «ጣጣጣጣጣ ..ጥጥጥጡዋ » ሲያደርጉት «ትግራይ ላይ ወያኔን ምታ !» ብለው ዞር ሲሉ አንድ ዱርዬ ተማሪ ከኋላቸው ቆሞ ያዩታል ። ከዚያም «ውይ ! ልጄ የት ነበርክ ?» ሲሉት «ጎጃምም ሲወጋ እዚሁ ነበርኩ : ጎንደርም ወያኔም ሲወጋ እዚሁ ነበርኩ» ሲላቸው : «ውይ ልጄ ! እናትም የለህ ?» ሲሉት ምን እንዳለ ታውቂያለሽ ? ቂቂቂቂቂ ... «ታዲያ እናት ቢኖረኝ ይታራብኛል እንዴ ?» ብሏቸው አረፈው እልሻለሁ።

ሃድጎ -አህያ ሸራህያ
1. ጋዜጠኛው አረፋይኔ ሀጎስ ስለ አለቃ ገብረ ሃና መጽሀፍ ጽፏል። ታዲያ አለቃ ከአጼ ተዎድሮስ ጊዜ ጀመሮ የነበሩ የቤተክርስቲያን ምሁር እንደሆኑ ነው መጽሀፉ የሚያወራው።ከጊዜው ቀልዳቸው አንዱ እንዲህ ይላል። በአጼ ተዎድሮስ ቤተመንግስት ሀድጎ የሚባል ባለሟል ነበረ ታዲያ ምንም እንኳን ንጉሱ ቀልድ የማያውቁ ኮስታራ ቢሆኑም አለቃ ግን መኮመኪያ ምክንያት አላጡም። እናም ሀድጎን ባገኙት ጊዜ ሁሉ ሀድጊ ብለው ነበር አሉ የሚጠሩት። አህያ ለማለት።ሀድጎም መረረውና ጃንሆይ ዘንድ ከሰሳቸው።. ንጉሱ አለቃን አስጠርተው ለምን ሀድጊ እያሉ እንደሚሳደቡ ቢጠይቋቸው አይ ጃንሆይ እኔ «አህያ ሸራህያ» እያልኩ ስጸልይ ሰምቶኝ እንጂ አልሰደብኩትም ብለው በብልሀት አመለጡ።


ጎመን እያበሰልሁ ነው
2. በእመቤታችን በፍስለታ ጾም አለቃ ቤተክርስቲያን አገልግለው ሲመለሱ ባለቤታቸው ማዘንጊያ የሚበላ ነገር በጎመን ይሰጧቸዋል ጎመኑ አልበስሎም ኑሮ ከምግብ በዃላ አለቃ ኆዳቸውን ወደሳቱ ጠጋ አድርገው ያሻሻሉ። ማዘንጊያ ነገሩ ገርሟቸው አለቃ ምን እያደረጉ ነው ይሏቸዋል አለቃም በአሽሙር ጎመኔን እያበሰልሁ ነው አሉ ይባላል።


አይ ጎራዴ አይ አስተጣጠቅ
3. አንድ የሚኒልክ መኮንን ስልብ ነበሩ ይባላል። መኮንኑ አንድ የጀግንነት ስራ ይሰሩና ሙሉ ትጥቅ ከነልብሱ ይሸለማሉ። አለቃን ያገኟቸውና “አለቃ እንዴት ነው?” “አላማረብኝም” ይላሉ።አለቃም መልሰው “አይ አስተታጠቅ አይ አለባበሥ አይ ጎራዴ አይ ጎራዴ አይ ጎራዴ” ይላሉ። ሌሎች መኳንንት መኮንኑን አለቃ ምን አሉህ? ይሉታል አደነቁኝ አይ አስተታጠቅ አይ ጎራዴ አሉኝ ይላል።መኳንንቱም ምን አደነቁህ ሰደቡህ እንጂ ስልብ ስለሆንክ ጎራዳ ነህ - አይ ጎራዴ -የኔ ጎራዳ ነው ያሉህ ብለው አብግነውት አለቃን ካልገደልኩ ብሎ በገላጋይ ነው አለቃ የተረፉት አሉ።


እንደምን አደራችሁ
4. አለቃ ሀሳባቸውን በሰምና ወርቅ በመግለጽ ጥበባቸው ተወዳዳሪ የላቸውም ይባላል። ታዲያ አንድ ቀን አንድ አውቃለሁ ባይ ሰውዬ ስለእርሳቸው ቅኔያዊ አነጋገር ምንም ቦታ እንደማይሰጥና በቅኔ ቢሰድቡት እርሱ ደግሞ ከዚያ በላይ በቅኔ መልሶ ሊሰድባቸው እንደሚችል ጉራውን ይነዛል። ጉራውንም የሰሙት ሰዎች አይ አንተ ሰው! ስለማታውቃቸው ይሆናል እንጂ የሚቻሉ አይደሉም። ይሰድቡሀል። ለማንኛውም ከፈለካቸው ወደገበያው መሄጃ መንገድ አከባቢ ስለማይታጡ ብቅ ማለት ትችላለህ ይሉታል። ሰውዬውም ቢያገኛቸው ለቅኔያቸው የሚሰጠውን መልስ እያሰላሰለ አህያውንም እየነዳ ወደ ገበያ ሲሄድ ያገኛቸዋል። ከዚያም ሰውዬው «አለቃ እንደምን አደሩ?» ይላቸዋል። አለቃም ትኩር አድርገው ያዩትና የተንኮል ሰላምታ መሆኑን በመረዳት «እግዚአብሄር ይመስጌን ደህና ነኝ! እናንተስ ደህና አደራችሁ ወይ?» ብለው በትህትና ለሰላምታው መልስ ሰጥተው ይሸኙታል። ሰውዬውም ስላልተሰደብኩኝ መስደብ የለብኝም ብሎ እየተኩራራ ይመለስና እነዚያን ሰዎች ያገኛቸዋል። ኧሃ ከአለቃ ጋር ተገናኛችሁ? ምንስ ብለው ሰደቡህ? ሲሉት እርሱም አይ ምንም አልሰደቡኝም እንዲያውም በትህትና ሰላምታ ተለዋወጥን። እኔን ሊሰድቡኝ አይችሉም ብያችሁ የለም? አለ። እስቲ እንዴት ነበር የተባባላችሁት ሲሉት አይ እኔ አለቃ እንዴት አደሩ ስላቸው እሳቸውም በትህትና አንገታቸውን ዝቅ አድርገው “እግዚአብሄር ይመስጌን እናንተስ እንዴት ናችሁ ነው” ያሉኝ አላቸው። ሰዎቹም ካንተ ጋር ሌላ ሰው ነበረ ወይ ሲሉት ኧረ የለም አህያዬን እየነዳሁ እሄድ የነበርኩ እኔ ብቻ ነበርኩኝ ሲላቸው አይ ወንድሜ ! አንድ ሰውማ እንዴት አደራችሁ አይባልም አንተን ከአህያህ ጋር አንድ አድርገው በመቁጠር ነው እንዴት አደራችሁ ያሏችሁ ብለው የሰውየውን መሸነፍ እና አህያ መባል አበሰሩለት አሉ።


እሱን ይጨርሱና
(5) አለቃን አንዲት ጉብል ነች አሉ ያሸነፈቻቸው።ዝናዋን ይሰሙና ልጅቱዋ ቤት ሄድው አሳድሩኝ ይላሉ። ቤት ለእንግዳ ይባሉና እራትም በልተው የሚተኙበትን መደብ ጉብሊቱዋ ታሳያቸውና ትንሽ አጎዛ (የበግ /የፍየል ቆዳ) አምጥታ ትሰጣቸዋለች። አለቃም ይቺማ ታንሰኛለች ሌላ ጨምሪልኝ ይላሉ። ጉብሉዋም እሱን ይጨርሱና አክልሎታለሁ አለቻቸው አሉ።


አሸነፈቻቸው
(6) እሩቅ አገር ሄደው መሽቶባቸው ከሚያውቋቸው ቤተሰብ ቤት ደርሰው አርፈዋል። ቤተሰቡም ካስተናገዳቸው በኋላ በይ መደቡ ላይ አንጥፊላቸው ብለው እናቱዋ ለልጂቱ ይነግሩዋታል። ልጅቷም የአንድ ትንሽ ፍየል አጎዛ ወስዳ ታነጥፍና ትመጣለች። አለቃ አንጥፌልዎታለሁና ሄደው ሊተኙ ይችላሉ ትላቸዋለች። ሄደው ሲመለከቱ አጎዛዋ እጅግ ትንሽ ከመሆኗ የተነሳ መደቡ መሐል ሆና አንሳ ትታያቸዋለች። ይሄኔ ይህች ድብዳብ እንድተኛባት መቼ ትበቃኛለች ይሏታል። ልጅቱም ስትመልስላቸው እሱን ከጨረሱ በኋላ እጨምርልዎታለሁ አለቻቸው ይባላል።


ሌላ እደግሞታለሁ
(7) አለቃ ገብረ ሀና እጅግ በጣም ታዋቂና በነገር እንደማይሸነፉ በብዛት ሲወራ ሰምቻለሁ አንድ ወጣት ኮረዳ ግን እንዳሸንፈቻቸው ይነገራል እስቲ .. አለቃ ወደመንገድ ሲሂዱ ይመሽባቸውና ወደሰው ቤት ጎራ ብለው የመሸብኘ መንገደኛ ነኝ ብለው ይጠይቃሉ። ባለቤቶቹም ቤት ለንግዳ ብለው ያስገቧቸዋል። ምግብ በላልተው መኝታ ደረሰ። አለቃ አይናቸው ቁልጭ ቁልጭ ሲል ኮረዳዋ «አለቃ ምን ፈለጉ?» ስትላቸው ልጄ ጎኔን የማሳርፈበት ነገር አምጪልኝ አሏት። እሷም እሺ ብላ አንድ የበግ አጎዛ ሰጠቻቸው። እሳቸውም «ምነው ልጄ ይህቺ ትበቃኝ» ሲሏት፤ «እሷን ሲጨርሱ ሌላ እደግምዎታለሁ» አለች ይባላል።


እያሳራኝ ነው
(8) አንድ ከዚህ በፊት የተረቡት ሰው መንገድ ላይ አግኝቷቸው ሊደብደብ ሲያባርራቸው እሳቸውም ሲሮጡ ቆይተው ሊደርስባቸው ሲሆን ቶሎ ብለው ሱሪያቸውን ፈተው ለመጸዳዳት ቁጭ ይላሉ። አለቃ በነበሩበት ዘመን ይትባሃሉ ሰው ጠላትም ቢሆን የሚገደለው፤ የሚደበደበው ከነሱሪው እንጂ ሱሪ አውልቆ አይደለም። ይሄ ወንድምነትም አያሰኝም። መለኛው አለቃ ይቺን ሰሩዋ። ሰውየውም ሊነርታቸው (ሊያሳራቸው) እስኪነሱ አጠገባቸው ቆሞ ይጠብቃል። እሳቸው ቁጭ እንዳሉ ሰውየው እንደቆመ ሁለቱን የሚያውቅ ሰው በመንገዱ ሲያልፍ ሰላም ብሏቸው የሁለቱ ነገር ገርሞት «ምን እያደረጋችሁ ነው?» ይላቸዋል። አለቃም ፈጠን ብለው «እያሳራኝ ነው።» ብለው መለሱ። ሊደበድባቸው የነበረው ሰውዬ በመልሳቸው ስቆ ትቷቸው ሄደ አሉ።


አለቃ ገብረ ሃና ሞቱ
(9) አለቃ በጣም ቸገራቸውና ልጃቸውን ሂድና ንጉስ ሚኒሊክን አባቴ ሞቶ ግን ተስካሩን የማወጣበት ገንዘብ የለኝም ብለህ ገንዘብ ተቀብለህ ና ብለው ላኩት። ልጅም እንደተባለው ወደ ቤተመንግስት ሂዶ ያባቱን ከዚህ አለም በሞት መለየት ነግሮ እንደተባለው ገንዘቡን ይጠይቃል። ምኒሊክም እጅግ በጣም አዝነውና አልቅሰው ገንዘቡን ሰጥተው ይልኩታል። አለቃም ችግራቸውን ከተወጡ በኋላ ምኒሊክን ሊያዪ ጉዞ ወደ አ.አ. ያቀናሉ። በቤተመንግስቱም ያያቸው በመገረም እን...ዴ? አለቃ ሞተው አልነበር በማለት እየተገረሙ ለምኒሊክ ሊነግሩ ተጣደፉ። ሚኒሊክም ሲያዩአቸው ገብረሀና ሞተህም አልነበር ቢሏቸው አለቃም እንደርሶ የሚስማማኝ ንጉስ ባጣ ተመልሼ መጣሁ ብለው ንጉሱን አሳቋቸው አሉ።


አሬን ስበላ ከረምሁ
(10) አለቃ የሚኖሩበት አካባቢ ድርቅ ጠንቶ ሁሉም ስደት ገባ።አለቃም ሲጓዙ ውለው ጥሩ አካባቢ ይደርሱና የግዜር መንገደኛ ነኝ ብለው አንዷን ባልቴት ለምነው ሊያድሩ ይፈቀድላቸዋል። ሌሊት ላይ ከመደባቸው ይነሱና ባልቴቱዋ ምኝታ ጋ ሄደው አይነ ምድራቸውን ተወጥተው ምኝታቸው ተመልሰው ባልቴቱዋን መጣራት ይጀምራሉ። ሴትየዋም «ምነው? ምን ሆኑ?» ስትላቸው ቤቱ አይነምድር አይነምድር ይሸታል እና መተኛት አቃተኝ ይላሉ። ሴትየዋም ኩራዟን ትለኩስና ፍለጋ ይጀመራል። አለቃም ተነስተው ወደ ባልቴቲቱ ምኝታ አካባቢ ሄደው እዚህ ነው እዚህ ነው ብለው ይጮሃሉ። «ኧረ ጉድ ኧረ ጉድ እንዴት ቤት ውስጥ ትጸዳጃለሽ ባይሆን እኔ አለሁ አይደል እንውጣ አትይኝም» ብለው ድምፃቸውን የበለጠ ከፍ ያደርጋሉ። ሴትየዋም ጎረቤት እንዳይሰማባት ብላ አለቃን ትለምናቸዋለች። ከዚያም ትንሽ አጉረምርመው አክርሚኝ ይላሉ። በዚህ ተስማምተው፤ አለቃም ከርመው ያ የድርቅ ወቅት ያልፍና ወደ ሀገራቸው ሲመለሱ የሚያውቃቸው ሰው አግኝቷቸው «እንዴት ከረሙ?» ይላቸዋል።አለቃም «አሬን ስበላ ከረምኩ» ብለው መለሱ አሉ።


አሬን ስበላ ከረምሁ
(11) አለቃ ገ /ሀና ከጎንደር አዱ ገነት አፄ ምኒልክ መናገሻ ለደጅ ጥናት ሰንቀው በወረሀው ፆም አካባቢ ይጓዛሉ። ጥኌት ወደ ቤተ መንግስት የወጡ ማታ ወደ ማደሪያቸው እየተመላለሱ የወረሀውን ፆም ጨርሰው ፍስክ ሲገባ ወደ ጠጅ ቤቶች ጎራ እያሉ መልከስከስ ይጀምራሉ። የያዙት ደረቅ ስንቅ አልቆ ወደ ማርትሬዛቸው ምንዘራ ጀምረዋል። ወርሀ ግንቦት ገብቶ ክረምቱ ሊጀምር ሲል ውሳኔ ላይ መድረስ ነበረባቸው --ደጅ ጥናቱን ትተው ወደ ጎንደር ማቅናት ወይም እየተሟጠጠች ያለችውን ኪሳቸውን የሚያደልቡበት መንገድ መፈለግና ክረምቱን አራዳ ማሳለፍ፤ ደጅ ጥናቱንም መቀጠል። ታዲያ አንዷን የጠጅ ኮማሪት መሳም ከጀመሩ ቀኖች ተቆጥረዋል። አንድ ምሽት ግን ተንኮል አዘጋጅተው ኖሮ እሆን ብለው እዳሪያቸውን ሳይወጡ አብረው ይተኛሉ። ከሥራ በኌላ (ከመሳሳም በኌላ) እንቅልፍ መጥቶ የምኝታ ጓደኛቸውን እየረፈረፈ ሳለ፤ አለቃ ቀ .. ሰ . ስ ብለው ከጠፍር አልጋው እራቅ ብለው ይኮሱና ይዘውት ወደ አልጋው ቀ --ሰ --ስ ብለው ይጋደማሉ። ከዚያ የምኝታ ጓደኛቸውን (የጠጅ ቤቱን) ባለቤት መቀመጫ አካባቢ አብሰው የቀረውን ባካባቢው ያልከሰክሱታል። ሊቆዩ አስበው ሽታው ስላስቸገራቸው ሴትዮዋን መቀስቀስ ይገባሉ። ምነው ብለው ሲነቁ ሽታው እያድቀሰቀሰ የሚያመራው ወደሳቸው ጉያ መሆኑን የተገነዘቡ ኮማሪት። አለቃን። ስለፈጠረዎ በማሪያም ይዠወታለሁ። የሚፈልጉትን ሁሉ አደርጋለሁ። ከመሀላችን እንዳይወጣ ማለት። ደጅ ጥናቱንም ቢሆን እስከሚሳካልዎ እዚሁ ከኔ ጋር መቆየት ይችላሉ አሏቸው። አለቃም አይዞሽ ምንም ችግር የለም ያለ ነው። አትሰቀቂ ብለው ያረጋጓታል። በዚህ አስባብ አለቃ ወደ ጎንደር ሳይዘልቁ ክረምቱን ያለምንም ችግር ያሳልፋሉ።በአዲሱ ዓመት መጀመሪያ አካባቢ ደጅ ጠኙ ሁሉ ምኒልክ ግብር ሲገባ እሳቸውም ይገኛሉ። በመገኘታቸው የተገረሙ አፄ ምኒልክም «እንዴ አለቃ እዚህ ምን ስትበላ ከረምህ?» ብለው ሲጠይቋቸው ህ ..ም ብለው «አሬን ስበላ ከረምሁ።» ብለው መመለሳቸውን ሰምቻለሁ።


አምባው ተሰበረ
(12) አለቃ ድንግላዊ መነኩሴ ነበሩ። በእነ አለቃ ዘመን ወይዛዝርት መነኩሴዎችን ካሳቱ ለነሱ ወይ ለቤተሰቦቻቸው የግብር ምህረት ይደረግላቸዋል አሉ። እንደጀግናም ይወደሳሉ። ሰለዚህ መነኩሴን ለማሳት እና ለመገናኘት የማይደረግ ጥረት የማይፈነቀል ድንጋይ የማይቧጠጥ ዳገት የለም። እንደሚታወቀው የታቦት ንግስ ቀን ድግስ በየቦታው ይኖራል።ካህናትም ይጠራሉ ይባርካሉ ይበላሉ ይጠጣሉ።አንድ ቅዳሜ ቀን በዋለ ንግስ እለት የእነአለቃም የካህናት ቡድን ከቀትር በኋላ ወደእነማዘንጊያ ቤት ተጉዞ ሲበሉ ሲጠጡ ሲጫወቱ ውለው አመሻሹ ላይ ድንግላዊው መነኩሴ ገብረ ሃና መጠጥ አዳክሟቸው ኖሮ ካህናት ጓደኞቻቸው እና የማዘንጊያሽ ቤተሰብ ይስማሙና አለቃ እዚያው እንዲያድሩ ትተዋቸው ይሄዳሉ። አለቃም አደሩ። አዳራቸው ግን የወትሮው አልነበረም። ከማዘንጊያ ጋር ነበር። ማዘንጊያም እንደጎጃሞች አምባው ተሰበረ እንደነጅበላ ይፈር የነበረ አሉዋ። መነኩሴው ድንግልናቸውን አፈረሱ። በማግስቱ አለቃ አዝነው ወደ ሚያገለግሉበት ቤተ ክርስቲያን ሄደው የደረሰባቸውን ተናገሩ። ካህናቱም ምን ሲደረግ አሉ። አለቃም የእናንተስ ስራ ተገቢ ነው ጓደኛ ጥሎ መሄድ አሉ። አለቃና ማዘንጊያም ተጋቡ።


አለመመጣጠን
(13)ማዘንጊያን ካገቡ በሁዋላ የቁመታቸው ያለመመጣጠን ችግር ፈጥሮባቸው ነበር ይባላል። አለቃ በጣም አጭር ማዘንጊያ በጣም ረጅም! ታዲያ ሲራ ሲጀምሩ ቢያንስ ከማዘንጊያ ግማሽ አካል በታች መውረድ ግዴታቸው ነበር። በስራ ወቅት መሳሳምም ሆነ ማውራት አይመቻቸውም። ስለዚህ ስራ ሊጀምሩ ሲሉ በይ ማዘንጊያ ደህና ሰንብቺ እኔ ወደ ቆላ መውረዴ ነው ብለው ይሰናበታሉ ይባላል።


አለቃ ወረኃና በጣም አጭር - ድንክዬ ሰው ናቸው
(14)ሚስታቸው ወይዘሮ ማዘንጊያሽ ደግሞ ሲበዛ 1ሜትር ከ80 ናቸው። መንገድ ውለው ወደቤታቸው ሲመለሱ ወይዘሮ ማዘንጊያሽ ሠማዩን አይተው አለቃ ዝናብ ሊዘንብ ነው መሰለኝ ይሏቸዋል። ከዚያ አለቃ ከኋላቸው ኩስ ኩስ እያሉ ሲመልሱላቸው! «እኔ ምን አውቃለሁ ለሰማዩ ቅርቡ አንቺ ነሽ» አሏቸው ይባላል።


ገብተሽ አልቀሽ
(15)አንድ ቀን ከወዳጃቸው ዘንድ ድግስ ተጠርተው ሄደው እዚያ ውለው ወደ ቤታቸው ሲመጡ አሽከራቸው በር ሲከፍት አስቀደመው አለቃ ገብተው የባለቤታቸውን መግባት ሲጠባበቁ ትንሽ ዘግየት ስላሉ «እባክሽ ገብተሽ ገብተሽ አልቀሽ እንደሆን በሬን ልዝጋበት» አሉ። የቁመታቸውን መርዘም መናገራቸው ነው።


ለሰማይ የምትቀርቢ
(16)ወ /ሮ ማዘንጊያ የአለቃ የህግ ሚስት ረጅም ነበሩ። መንገድ አብረው ሲሄዱ ወ /ሮ ማዘንጊያ ወደ ሰማይ ያዩና «አለቃ ዝናብ የሚዘንብ ይመስሎታል ብለው ይጠይቃሉ»። አለቃም ሲመልሱ “ለሰማይ የምትቀርቢ አንቺ አይደልሽም እንዴ?” “እኔ ምኑን አውቀዋለሁ” ብለው ባለቤታቸውን በቁመታቸው ምክንያት ተረቧቸው።


እዚያም ቤት እሳት አለ
(17)አለቃ የጎረቤት ፍቅር ይጀምሩና ባለቤታቸው ወ /ሮ ማዘንጊያ ዉኃ ሊቀዱ ሲወርዱ ጎረቢት ፍቅርን ልትቃመስ ትመጣለች። መጥታም ከአለቃ ጋር ሲንጎዳጎዱ ሳያስቡት ወ /ሮ ማዘንጊያ ቢደርሱባቸው ውሽምዬም ከመደንገጧ የተነሳ ልጅዋን ያነሳች መስሏት ያለቃን ልጅ አንጠልጥላ ትሮጣለች። ነገሩ የገባቸው ማዘንጊያም ልጁን አንስተው «አሁን እዚህ እሳት ውስጥ ልክተተው?» ቢሏቸው አለቃም ማዘንጊያ እዚያም ቤት እሳት አለ ብለው ልጁን አተረፉ አሉ። ከርታታ (Jun 11, 2005)


በጃቸው
(18)አለቃ በጣም ሴሰኛ መሆናቸው ይነገራል። በአንድ ወቅት አንዲት ወጣት አይተዋት በመውደዳቸው ወላጆችዋን እንደምንም ብለው በማስፈቀድ ያገቧታል። አንሶላ የመጋፈፊያው ጊዜ ሲደርስ አለቃ ወረድ ብለው ስራ ሊጀምሩ ሲሉ እንትናቸው ተኝቶ አልነሳ እምቢ ይላቸዋል። ቢታገሉ ቢታገሉ አልተሳካላቸውም። ስለዚህ ሌላ አማራጭ በመውሰድ ለእጃቸው ተጨማሪ ስራ ሰጥተው ሲያሰሩ ያድራሉ። መከራዋን ስታይ ያደረች ልጅም ጠዋት ለሽንት እንደወጣች በዚያው ጠፍታ ወደ ወላጆችዋ ትሄዳለች። ችግሯን ግን ደፍራ አልነገረቻቸውም። ይሁንና አለቃ ሳያፍሩ ሽማግሌ ሰብስበው ወደ ልጂቱ ቤት ይመጣሉ። ሽምግልናም ይጀመራል። ለምን ትተሻቸው እንደመጣሽ፤ ምን እንደበደሉሽ ንገሪን ትባላለች። እንዴት ደፍራ ትናገር! ተቸገረች። በመጨረሻም ሲያዋክቧት ግራ ገባትና በእጃቸው .....ብላ የሚቀጥለውን መጨረስ ሳትችል ትቀራለች። አለቃም ምን ለማለት እንደፈለገች ይረዱና ወዲያውኑ ለሽማግሌዎች እስቲ እግዜር ያሳያችሁ! ድሮውንስ ላይበጀኝ ነው ያገባኋት በጃቸው የምትለኝ? ብለው ለጊዜው ጉዳቸው ሳይወጣ አሸንፈው ወሰዷት ይባላል።


ደርቆ ተንጣጣ
(19)አንድ ሰሞን አለቃ በጣም ቆንጆ ልጅ ያገባሉ። ከዚያም ያው እንደ ባህል ወጉ ልጂቱ እሳቸው ጋ ልታድር ቤታቸው ትሄዳለች። እናም ቀኑ ተገባዶ ማታ ላይ አለቃ ቆጥ ላይ ወጥተው ሲጠብቋት እሷ ማታ ወደ ቤተሰቦቿ ከድታ ልትሮጥ ከቤት ስትወጣ ውጪው እንደአጋጣሚ ዝናባማ ስለነበር አድልጧት ትወድቅና ተመልሳ ቤት ትገባለች። ቤት ገብታም ምድጃ ዙሪያ ተቀምጣ ልብሷን ስታደርቅ ሳት ይላትና ጡጥ ታደርጋለች። ይህን የሰሙት አለቃ «አንቺ አትተኝም?» ይሏታል። እሷም «እስኪ ይቆዩ ልብሴ ምጥጥ ምጥጥ ይበልልኝ» ትላለች። እሳቸውም እሺ ብለም ዝም ሲሉ ልጂቱ አሁንም ደግማ ዛጥ ታደርጋለች።በሁኔታው የተቆጡት አለቃ በስጨት ብለው «አንቺ አትተኝም?» ሲሏት። እሷ «እስኪ ይቆዩ...ልብሴ ይድረቅ ትላለች።» ከዚያም አለቃ ቀጥለው «ኧረ ...ኤዲያ ...ልብስሽ ደርቆማ እየተንጣጣ» ብለው ባሽሙር ጠቅ አረጓት ይባላል።


እሷ ትታቀፋለች
(20)የመሸባቸው መንገደኞች አለቃ ገብረሀና ቤት ምሽቱን ለማሳለፍ ይጠይቁና እንደ ባህሉ አለቃ “ቤት ለእንግዳ” ብለው ማደሪያ ይሰጧቸዋል። እንግዶቹም ፈረሶቻቸውን እደጅ አስረው ይገባሉ። አለቃንም «እባክዎ ፈረሶቹ እርቧቸዋልና ሳር ይስጡልን» ብለው ይጠይቃሉ። አለቃም «ምን ችግር አለ ታዲያ ከውጭ አጭጄ አመጣላቸዋለሁ» ይላሉ። ነገር ግን የአንዱ እንግዳ አይን ማዘንጊያ ላይ ሲቁለጨለጭ ያጤኑት አለቃ፤ ነገሩ ስላላማራቸው ማዘንጊያን ነይ እስቲ ተከተይኝ ይላሉ። እንግዶቹም«ለምን እሳቸውን (ማዘንጊያን) ያደክማሉ?» ብለው ይጠይቃሉ። አለቃም «አይደለም እኮ እንዲያው እኔ ሳጭድ እርሷ ትታቀፋለች ብዬ ነው» በማለት ስጋታቸውን በዘዴ ገለጹ።


ውዳሴ ማርያም ልደገም
(21)አለቃ ገብረሀና የማይለመድ ለምደው ማታ ማታ ሰራተኛቸው ጋ ብቅ ሳይሉ አያድሩም ነበር። አንድ ቀን ሰራተኛቸው ጋ አምሽተው ቆይተው ቀስ ብለው ተደብቀው ገብተው ይተኛሉ። ትንሽ እንደቆዩ እንደገና ያምራቸውና ቀስ ብለው ምንም ሳያሰሙ እራቁታቸውን ሊሄዱ ሲነሱ ወ /ሮ ማዘንጊያ ነቄ አሉና «አንቱ ወዴት ኖት በዚህ በጭለማ» ብለው ወይዘሮ ማዘንጊያ ሲጠይቋቸው። «ቆዪ እስኪ አንዴ ውዳሴ ማርያም ደግሜ ልምጣ»አሉ። «ታዲያ ውዳሴ ማርያም እራቆት ተኩኖ ነው የሚደገም?» «ምን ላድርግ? እራቁቴን ሆኜ እንኳን ብትሰማኝ» ብለው እርፍ።


ቁጭ ብዬ ሳመሽ
(22)ውሽምዬ አለቃ ሲወጡ ቤት ይመጣል እና ተማዘንጊያ ጋር ተላምደው ኖሯል።አለቃ ከውጭ ድክም ብሏቸው መጥተው ደጃፍ ያለች መደብ ላይ ቁጭ ብለዋል። ማዘንጊያም ከውሽምዬ ጋር የስንብት ሲሳሳሙ አለቃ አይተው ዝም ብለዋል። ውሽ...ም በጓሮ ተሸኝቶ ማዘንጊያ ወደ ደጃፍ ብቅ ሲሉ አለቃን ያዩዋቸዋል። «አለቃ መጥተዋል እንዴ?» ይላሉ። «እንዴ እዚህ ቁጭ ብዬ ሳመሽ አላየሽኝም እንዴ» ብለው ማዘንጊያ ሲሳሙ ማየታቸውን ተናገሩዋ። ታዲያ ይሙቱ እንዴ ታፍነው?


ጉድ ባይ ብዬ መጣሁ
(23)አለቃ ከስራ በጣም ደክሟቸው ያለሰአት ወደ ቤት ይመጣሉ። ልክ እቤት እንደደረሱ ወ /ሮ ማዘንጊያ ሲያቃትቱ ሰምተው መቋሚያቸውን ጠበቅ አድርገው ወደ ቤት ሳያንኳኩ ..ሰተት ይላሉ ልክ እንደገቡ የሳቸው [የአለቃ] ቅርብ ጓደኛቸው አልጋቸው ላይ ከማዘንጊያ ጋር ጉዳዩን ተያይዞት ያያሉ። አለቃም ተገርመው «እና...ንተ» ቢልዋቸው። ማዘንጊያሽ እና ጓደኛቸው ደንግጠው «አለቃ ምነው ያለሰአቶ» ቢሏቸው እሳቸውም መልሰው «የስራ ባልደረቦቼን ጉድ ባይ ብዬ መጣሁ» አሉአቸው።


አስበጂና ላኪልኝ
(24)የአለቃ ገብረሀና ጎረቤት የሆኑት አንዲት ወ /ሮ የአለቃን ባለቤት ወ /ሮ ማዘንጊያን ከአንድ ጎበዝ ጋር አስተዋውቃ ሁለቱ በየጊዜው ከቤቷ እየተገናኙ የልባቸውን ይወያያሉ። ከእለታት አንድ ቀን አለቃ ቤተ ክርስቲያን ተሳልመው ሲመለሱ ቤታቸው የፊጥኝ ታስሮና ተዘግቶ ስላገኙት ባለቤታቸው ወ /ሮ ማዘንጊያ ወዴት አንደሄዱ ጎረቤታቸውን ይጠይቋታል። እርሷም «መደብ እየሰራሁ ስለሆነ ማእዘኑን እያበጀችልኝ ነው» በማለት መልስ ትሰጣለች። እርሳቸውም “ቡና ስለጠማኝ ቶሎ አስበጅና ላኪልኝ” በማለት ትክክለኛውን መልእክት በዘዴ አስተላለፉ አሉ።


ማን ደፍሮ ይገባል
(25)አለቃ ሚስታቸው የቂጥኝ በሽታ ይዟቸው ወሸባ ገብተው (የቤት ውስጥ ህክምና ) ከቤት ተኝተዋል። በሽታውን ማን እንዳስያዛቸው ሲመረመሩ ማንደፍሮ የሚባል የመንደር አውደልዳይ መሆኑን ሰምተዋል። ታዲያ አንድ ወዳጃቸው የሆነ ሰው «ኧረ ለመሆኑ ከርስዋ ቤት ማን ገብቶ ነው ሚስትዎን ቂጥኝ ያስያዛቸው?» ብሎ ቢጠይቃቸው «አዬ ወንድሜ ያስያዛትንማ ማን ብዬ ልንገርህ ከኔ ቤት ማን ደፍሮ ይገባል?» ብለው መለሱለት ያስያዛት ማንደፍሮ ነው ማለታቸው ነው።


ምልምሎች
(26)ለእንጦጦ ማርያም ይመስለኛል ጣይቱ ለመዘምራንነት ድምጸ መረዋ የሆኑ ስልቦችን ለአገልጋይነት ይሰጣሉ። እነዚህ መዘምራን ከአለቃ ጋር በምን እንደተጣሉ አይታወቅም። አለቃ እነሱን እናንተ ምልምሎች ይሏቸዋል። መዘምራኑም ምኒልክ ዘንድ ይከሳሉ ተሰደብን ብለው። አለቃም ተጠርተው ሲጠየቁ አልተሳደብኩም ይላሉ። ከዚያ ምን ብሎ ነው አለቃ የሰደባችሁ ይላሉ ምኒልክ። መዘምራኑ አፍረው ዝም ሲሉ አለቃ ምን ትላለህ ይሏቸዋል። አለቃም አልተሳደብኩም እቴጌ ጣይቱ ከአገልጋዮቻቸው መካከል መርጠው መልምለው ለእንጦጦ ማርያም ስለሰጡ ነው ምልምሎች ያልኩት አሉ። ምኒልክም ስቀው ዝም አሉ አሉ።


ጭን እያነሱ መስጠት
(27)የምኒልክ ወዳጅ የሆኑትን አለቃ በተረባቸው እትጌ ጣይቱ በጣም ይጠሏቸው ነበር አሉ። እናም አንድ ቀን በአል ነበር በአሉን ረሳሁት ለአለቃ እቴጌ አንድ የበሬ ንቃይ ይልኩላቸዋል። አንድ ጊደር ወይም ወይፈን የጠበቁት አለቃ በተላከላቸው የበሬ ንቃይ እግር (ጭን) ተናደው። «አይ እተጌ እንዲያው ለሰው ሁሉ አንዳንድ ጭን እያነሱ እየሰጡ ለምኒልክ ምን ሊተርፋቸው ነው? አይይ ኧረ ይሄን ለማንም እግር እያነሱ መስጠቱን ቢተውት ይሻላል።» ብለው በመናገራቸው ከምኒሊክ ቤተመንግስት ለመጨረሻ ጊዜ ተባረዋል።


ዋናውን ይዘው
(28)አለቃ በቀልዳቸው በመወደድም ይሁን በመፈራት የሚፈልጉትን የማግኘት እድላቸው ሰፊ ነው ይባላል። በመሆኑም አንድ ለቤተመንግስት ሰዎች ቅርብ የሆኑ ታዋቂ እመቤት ቤት በእንግድነት ይገቡና በዚህም በዚያም ብለው በድብቅ ከእመቤቲቱ ጋር ወሲብ ይፈጽማሉ። ከዚያም ለካ ባልጠረጠሩበት መንገድ ሚስጥሩ ሾልኮ ቤተክርስቲያን ከባልደረቦቻቸው ጆሮ ገብቶ ባልደረቦቻቸውን አስቆጥቷቸዋል። አጅሬ ይህን ጉድ ሳይሰሙ እንደልማዳቸው ስራቸውን ሰርተው አድረው ጠዋት አገልግሎት ሊሰጡ ወደ ቤተክርስቲያን ሲሄዱ ቀሳውስቱ ተመካክረው ከሴት ጋር አድረው መጥተው ቤተክርስቲያናችንን ሊያረክሱብን አይገባቸውም ብለው ሰድበው ያብርሯቸዋል። አለቃም ባጋጠማቸው ነገር አዝነው ከቤተክርስቲያኑ ይወጡና ካጥር ውጪ ድንጋይ ላይ ቁጭ ብለው ዳዊታቸውን እየደገሙ ሳሉ እመቤቲቱ ፈረስ ላይ ቁጭ ብለው ከነአጃቢያቸው ይመጡና ከፈረሱ ወርደው ወደ ግቢ ያመራሉ። በዚህን ጊዜ አለቃ ብድግ ይሉና «በንጉስ አምላክ ይመለሱ! ወደ ውስጥ ሊያልፉ አይገባዎትም» ብለው ይጮሀሉ። ሰው ግራ ገብቶት «ምነው አለቃ ! ምን እያሉ ነው?» ሲል እሳቸውም ምንም የሌለው ምስኪን ካልተፈቀደለት እሳቸው ዋናውን ይዘው እንዴት ሊገቡ ይችላሉ?» በማለት ለሴትየዋ በሚገባ ዘዴ ተናግረው በማሳፈር መለሷቸው ይባላል።


እኔ ለነካሁት
(29)አለቃ እንዲሁ ሴት ጋር ያድሩና ጠዋት ቤተክርስቲያን ሲሄዱ ይከለከላሉ እንዳይገቡ ያያቸው ሰው ስለነበር። እናማ በሴቶች በር በኩል ሄደው ዛሬ ሴቶች አይገቡም እዚህ ከገርገራው ውጪ ሆናችሁ ጸልዩ ብለው ሴቱን ሁሉ ከልክለው ካህናቱ ገርሟቸዋል አንድም ሴት ሳያዩ በመቅረታቸው። «ምን ሆነው ነው?» ሲሉ አንድ ያለቃን ስራ ያየ ካህን «አለቃ ከልክለው ነው ሴቶች እንዳይገቡ» ብሎ ያስረዳል።አለቃም ተጠርተው ሲጠየቁ «እኔ ለነካሁት ከተከለከልኩ እነሱ ይዘው እንዴት ይግቡ» ብዬ ነው አሉ።


መውጫችንን ነዋ
(30)ቦታው የት እንደሆነ አላውቅም ብቻ ጣይቱ በእንጨት ደረጃ ወደ ፎቅ ይወጣሉ። ድሮ ያው ግልገል ሱሪ አልነበረም ፎቅ ሲወጡ አለቃ ደረጃው ስር ሆነው አንጋጥጠው የጣይቱን ምስጢር ያያሉ። ጣይቱም መለስ ብለው ወደታች ወደ አለቃ አዩና አለቃ «ምን እያዩ ነው?» ቢሏቸው። «መውጫችንን ነዋ» አሏቸው።


ኩኩሉ
(31)መኳንንቱ በአለቃ ፍጥነት የሰላ አቃቂር ምን እናድርግ ብለው መከሩ። ነገ ሁላችንም እንቁላል ይዘን እንምጣና አለቃን እናፋጣቸው ብለው ተስማምተው በማግስቱ ጉባኤ ሁሉም ከኪሱ እንቁላሉን ብቅ ሲያደርግ አለቃም በቅጽበት እጃቸውን አርገፈገፉና ኩኩሉ አሉ። ከዚያም ለጥቀው ይህንን ሁሉ እንቁላል ያስወለድኩት እኔ ነኝ አሉ ይባላል። መኳንንቱ ሁሉ ሴት ዶሮ ሆነ።


በጠማማ ጣሳ
(32)በአለቃ ተረብ በተደጋጋሚ ጥቃት ደርሶበት በቁጭት ላይ የነበረ ሰው እርሳቸውን የሚተርብበት ጥሩ አጋጣሚ በማግኘቱ እጅግ በጣም ደስ ይለዋል። ይሄውም አለቃ እሰው ቤት እንጀራ በምስር ወጥ ተጋብዘው እስኪጠግቡ ይበሉና በወጡ የተለቃለቀውን አፋቸውንም ሆነ ከንፈራቸውን ሳይታጠቡ ሰው ወደተሰበሰበበት አደባባይ ይመጣሉ። ሰውዬውም ያገኘውን አጋጣሚ በመጠቀም በሰው ፊት አዋርዷቸው ዝና ሊያገኝ በመጣደፍ፤ «አለቃ! በዛሬው ገበያ የምስር ዋጋ ምን ያህል ነበር?» ይላቸዋል። አለቃም የሰውየውን ተረብ በቅጽበት ይረዱና ቀና ብለው ሰውየውን ሲያዩት ጉንጩ በጣም የከሳና የተጣመመ መምሰሉን ይረዳሉ። ታዲያ ለሰውየው የሚሰጡት መልስ ምን መሰላችሁ። «አይ ልጄ! ምስርማ ዛሬ ተወዶ በጠማማ ጣሳ በብር አንድ ሲሸጥ ውሏል።» በማለት የጉንጩን መጣመም ጠቆም አድርገው ቆሽጡን አሳረሩት ይባላል።


አስደግፈውት አመለጡ
(33)አለቃ መቼም ሲናገሩ ለነገ የለም እና አንዱን ዲያቆን አበሳጭተውት ሊደበድባቸው ይፈልጋቸዋል።እናም አንድ እለት በሩቅ ያዩትና ሮጠው እንደማያመልጡት ሲገባቸው ቶሎ ሮጥ ብለው አንድ ዘመም ወዳለ ጎጆ ይሄዱና ሊወድቅ ያለውን የጎጆውን ግድግዳ በጃቸው ደግፈው እንደቆሙ፤ ዲያቆኑ ይደርስባቸውና ምን እያደረጉ እንደሆነ ይጠይቃቸዋል። እሳቸውም ግድግዳው ሊወድቅ ስለሆነ ደግፈው መቆማቸውን እና እሱ ቢተካላቸው አጣና አምጥተው ግድግዳውን እንደሚያስደግፉ ነግረውት እሱ ሲተካላቸው አለቃ አስደግፈውት አመለጡዋ። አይ የያዛቸው ቀን እኔ የለሁበትም ቆርጦ ቆርጦ ነው የሚጥላቸው።


በሰው አገር ቀረሁ
(34)አለቃ መንገድ ወጥተው ይመሽባቸውና የመሸበት እንግዳ ብለው ሰው ቤት ይጠጋሉ። በኋላም ያረፉባት ሴትዮ ያለቃን ተረብ ታውቅ ኖሮ ተጨንቃ ተጠባ አሳ ወጥ ሰርታ እራት ታቀርባለች። ያው ሴትየዋም አሳው ወጥ ላይ የማይገባበትን ውሀ ጨምራበት ነበርና ትንሽ ቀጠን ብሎ ነበር። ታዲያ አለቃም የቀርበላቸውን እራት ጥርግ አድርገው ከበሉ በኋላ ለቅሶ ይጀምራሉ። እንደው ያዙኝ ልቀቁኝ ሰዎቹም ተጨንቀው አረ አለቃ ምነካዎ? ብለው ቢጠይቁ «አዬ አሳ አገሩ ሲገባ እኔ በሰው አገር ቀረሁ» ብለው የሴትየዋን የአሳ ወጥ በደንብ አለመስራት ተናገሩ።


ከአልጋ ላይ ወድቄ ነው
(35)አለቃ አንድ ቀን መንገድ መሽቶባቸው አንዲት ሴትዮ ቤት እንድታሳድራቸው ለምነው ቤት ለእንግዳ ብላ አስገባቻቸው። አለቃ ያው እንደሚተረከው ቅንዝራም ቢጤ ናቸው። እራት በልተው ከጨረሱ በኋላ በሉ እኔ መደብ ላይ እርሶ መሬት ላይ ተኙ ብላቸው ተኙ። ከዚያ ጨለማን ተገን በማድረግ ሴትየዋ መደብ ላይ ዘፍ ብላው መዳሰስ ይጀምራሉ። ሴትየዋም በድንጋጤ ነቅታ እንዴ ምን እየሰሩ ነው ስትላቸው ከአልጋ ላይ ወድቄ ነው አሏት። እንዴት መሬት ተኝተው ስትላቸው እኔንስ የገረመኝ እሱ አይደል አሏት ይባላል።


የተልባ ማሻው ሚካኤል
(36)አለቃ ከአዲስ አበባ ወደ ጎንደር ሲመለሱ ያው የግድ የአባይን በረሀ ማቋረጥ ነበረባቸው። አብረዋቸው የነበሩ መንገደኞች በቃ የአባይ ሽፍታ ሊዘርፈን ነው ብለው ሲያለቃቅሱ። አለቃ ብራችሁን ሰብስቡና አምጡ ብለው - መንገድ ሲሄዱ ተልባ እየወቀጡ የሚበሉበት ሙቀጫ ውስጥ ብሩን በሙሉ ይጨምሩና አፉን ወትፈው፤ ሙቀጫውን የቤተ ክርስቲያን ጨርቅ አልብሰው ለአንዱ መንገደኛ እንደታቦት አሽክመው ሲጓዙ ሽፍቶቹ ዘንድ ይደርሳሉ። ሽፍቶቹም ብቅ ብቅ ይሉና «ምንድናችሁ?» ይላሉ። አለቃም ፈጠን ብለው «ታቦት ልናስገባ ይዘን የምንመጣ መንገደኞች ነን» ይላሉ። አንዱ ሽፍታም «የታቦቱ ስም ማን ነው?» ይላል። አለቃም «የተልባ ማሻው ሚካኤል ነው» ብለው መለሱ። ሽፍቶቹም ተሳልመው መንገደኞቹም በሰላም በረሀውን አለፉ።


ወላሂ ኑ እንብላ
(37)አለቃ ከሩቅ ቦታ ወደ አገራቸው ሲመለሱ ሽፍቶች ሊደርሱባቸው ሲል ያላቸውን ገንዘብ አገልግል ውስጥ ከተው ጠበቁዋቸው። ለሽፍቶቹም ኑ እንብላ ወላሂ ጥሩ የዶሮ ወጥ ነው ቢሏቸው እኛ የእስላም ስጋ አንበላም ብለው ትተዋቸው ሔዱ ይባላል።


ግም ግም ሲል
(38)ሊቁ ገብረሀና በሀያ ስድስት ዓመታቸው ጎንደር ውስጥ ሊቀ ካህናት ሆነው ተሾሙ። በዚህ ጊዜ አንዲት ጎንደሬ ዘንድ ጠበል ተጠርተው ቢሄዱ የሚወጡት ሰዎች ሁሉ «ጠላው ጥሩ አይደለም» ሲሉ ይሰሙና ተመልሰው ወደቤታቸው ይሄዳሉ። ሴትዮዋም በመቅረታቸው አዝና ቤታቸው ሄዳ «ምነው አባ ጠበል ጠርቼዎት ሳይመጡ ቀሩ?» ብትላቸው “ኧረ መጥቼ ሰው ግም ግም ሲል ጊዜ ነው የተመለስኩት።” አሏት።


ቢሻን እንበላለን ቢሻን እንጠጣለን
(39)በሀገራችን እንደተለመደው ድግስ ካለ ቄሱም ሼሁም ሁሉም እንደየሀይማኖቱ ይጠራሉ። አዝማሪዎችም አይቀሩም። ስለዚህ የአለቃ ግዳጅ አንዱ ድግስ መሄድ ነው። ሴትየዋ ያው እንደነገሩ አሸር ባሸር የሆነ ድግስ ብጤ አድርጋ ኖሮ አለቃ ወጡም ቅጥንጥን ጠላውም ውሀ ውሀ ብሎባቸው ኖሯል። ደጋሽ መጥታ አለቃ ይብሉ እንጂ ትላለች። አለቃም «የመጣንበትን ቢሻን እንበላለን ቢሻን እንጠጣለን» ብለው የልባቸውን ተናገሩዋ ድግሱን የፈቀዱ መስለው።


ከመሶብዎ አይጡ
(40)ሰው መቼም ወዶም ይሁን ፈርቶ አለቃን ይጋብዛቸዋል። አንድ ቀን ሊጋበዙ ወደ አንዱ ቤት ጎራ ብለው እንደተቀመጡ ጋባዥዋ ሴት እንጀራ ለማቅረብ መሶቡን ከፈት ስታደርገው ትንሽ አይጥ ዘላ ትወጣና ትሰወራለች። አለቃም ይህችን ጠንቀኛ አይጥ አይተዋት እንዳላዩ ጸጥ ብለዋል። ርቧቸው ስለነበረ ከራሳቸው ጋር እየታገሉ እስኪበቃቸው ድረስ ይበላሉ። ከዚያም በመጨረሻ ማእድ ሲነሳ መመረቅ የተለመደ በመሆኑ እንዲህ ብለው ይመርቃሉ ;- በላነው ጠጣነው ከእንጀራ ከወጡ እ /ር ይስጥልኝ ከመሶብዎ አይጡ።


የመጣሁበት ነው
(41)አለቃ ገብረሀና አንድ ጣና ሀይቅ ላይ ካለ ደሴት ላይ የምትኖር ሴት ጸበል ቅመሱ ብላ ትጠራቸዋለች። አለቃም በጥሪው ቀን በጀልባ ተሳፍረው ከጥሪው ቦታ ይደርሳሉ። ነገር ግን ትንሽ አርፍደው ነበርና ብዙው ምግብ ቀድሞ በመጣው ተጋባዥ ተበልቶ ወደማለቁ በመቃረቡ ያለውን ወጥ እንደ ነገሩ ቀጠንጠን አድርጋ ነበር ሴትዮዋ ያቀረበችላቸው። ቢሆንም ግን አሁንም አሁንም ብቅ እያለች «አለቃ ይብሉ እንጂ» ትላለች። «እሺ....እሺ» ማለት የሰለቻቸው አለቃም በመጨረሻ እንዲህ ብለው ይመልሳሉ። «እንዴ እበላለሁ እንጂ ....ምናለ ይሄ እኮ የመጣሁበት ነው» ......... ውሀ ነው ለማለት ያክል።


ጠረር አርገሽ ቅጂው
(42)አለቃ አንድ ቤት በእንግድነት ሄደው ሳለ ጠላ ይጋበዛሉ። ጋባዥ የነበረችው ሴትዮም ጠላውን ልትደግማቸው ጎንበስ ብላ ስትቅዳ ንፋስ ፈሷ ያመልጣታል። አለቃም ሰምተው እንዳልሰማ ይሆናሉ። የቀረበላቸውን ሲጨርሱ ሴትዮዋ እንደገና መጥታ «አለቃ ልድገሞት» ትላለች። አለቃም «ልድገም ብለሽ ነው? በይ እስቲ እንደቅድሙ ጠረር አርገሽ ቅጂው» ብለው መፍሳቷን እንዳወቁ በዘዴ ተናገሩ።


ዝግንትሉ ሞልቷል
(43)አንድ ቀን አለቃ ግብዣ ተጠርተዉ ይሄዱና ምግብ ቀርቦ እየበሉ ሳለ ትል ያጋጥማቸዉና አኩርፈዉ እየበሉ ሳለ ጋባዡ በድንገት ይመጡና «ምነው አለቃ በደንብ ብሉ» ይሉዋቸዋል።አለቃም ተናደዉ ኖራልና «እሺ ጌቶች እየበላሁ ነው። ምን ጠፍቶ ዝግን ትሉ እንደሆን ሞልቷል።» አሉ ይባላል።


ጥፍር ያስቆረጥማል
(44)አንድ ቀን አለቃ በእንግድነት ሰው ቤት ይሄዱና ምግብ ይቀርብላቸዋል። እየበሉ ሳለ በድንገት ከምግብ ጋር የገባ የጥፍር ቁራጭ ያገኙበታል። ከዚያም ባልቴቷም ትመጣና «አለቃ ብሉ እንጂ አይጣፍጥም እንዴ?» ትላቸዋለች።አለቃም የተቋጠረ ፊታቸውን ፈታ በማድረግ «ኧረ ይጣፍጣል ከመጣፈጥም አልፎ ጥፍር ያስቆረጥማል!!» አሉ አሉ።


የጓደኛህን ቀን ይስጥህ
(45)አለቃ ገብረ ሀና ከሸዋ ወደ ጎንደር ግብዣ ተጠርተው ግብዣው ላይ ለመገኘት ይጓዙና ጎጃም ላይ ሲመሽባቸው ወደ አንድ ኮማሪት ቤት ይገቡና መጠጥ አዘው ቁጭ ይላሉ። አለቃ ደርባባዋ ኮማሪትዋ ቃ ትላቸውና እዛ ለማደር ያስባሉ። በጣም ሲመሽም ኮማሪትዋ ሌሎቹን ሰዎች ታስወጣና አለቃን አይታ እኚሕ ሽማግሌስ ምንም አያደርጉኝም ብላ ለሳቸው መደብ ላይ አንጥፋ ከጎናቸው ፈንጠር ብላ ትተኛለች። በነገራችን ላይ ሴትየዋ አንድ እግሯ የተቆረጠ እና በአርተፊሻል እግር ነበር የምትራመደው። አለቃም ለሊት ላይ ወደ ሴትየዋ ተጠግተው አሰስ ዳሰስ ማድረግ ሲጀምሩ ሴትየዋም ነቅታ በደህና እግሯ በርግጫ ብላ ትመታቸዋለች። አለቃም ቀበል ያደርጉና «የጓደኛህን ቀን ይስጥህ ሌላ ምን እላለሁ» ብለው እርፍ።


በቁሜ ቀምሼ መጣሁ
(46)አለቃ ድግስ ተጠርተው አረፋፍደው ድግስ ቤቱ ቢደርሱ ሰዉ ሁሉ ተሳክሮ በብርሌ ሲፈነካከት ይደርሳሉ። ገና በሩን ገባ ከማለታቸው አንድ የተወረወረች ብርሌ ግንባራቸውን ትላቸዋለች። አይ ከዚህስ ቢቀርብኝ ይሻላል ብለው ወደ ቤታቸው ሲመለሱ አንድ የሚያውቁትን ሰው መንገድ ላይ ያገኛሉ። ሰውየው «አለቃ ድግሱ እንዴት ነበር?» አለቃም «በጣም ቆንጆ ነበር። ቶሎ ሂድ እንዳያመልጥህ እኔ እንኳን አንድ በቁሜ ቀምሼ መጣሁ» ብለውት እርፍ።


ሺ ነዋ
(47)አለቃ ገብረሃና አጤ ምኒልክ ግብር ሊበሉ ሄዱ። ተበልቶ ተጠጥቶ ለሽንት መውጣት አይፈቀድም ነበር። አለቃ ግን እወጣለሁ ብለው ተወራረዱ። ዘበኞች አናስወጣም ቢሏቸው «እምዬ ምኒልክ ለሽንት እንድወጣ ፈቅደውልኛል አሉ።» ዘበኞቹ «አይደረግም አሉ።» አለቃ «በሉ ንጉሱ ምን እንደሚሉ ስሙ አሉዋቸው።» ወደእምዬ ምኒልክ ጠጋ ብለው በጆሮዋቸው አንሾካሸኩ። «"500+500" ስንት ይሆናል?” እምዬ ምኒሊክም ሂሳብ አይችሉም እንዳይባሉ ጮክ ብለው «ሺነዋ» አሉ። አለቃም «ሺነዋ (ሽናው ) ተብዬአለሁ» ብለው ወደሽንት ቤት ሄዱ።


ቡሊ የአለቃ አህያ
(48)አንዴ አለቃ ቤት ጅብ ይገባና አህያቸው ቡሊ በፍርሀት ጩኸቱን ያቀልጠዋል። ሚስታቸው ማዘንጊያ አለቃን ቀስቅሰው ጅቡን እንዲያባርሩ ቢንግሯቸው «ባክሽ እኔ እፈራለሁ» በማለት አለቃ ሲመልሱ ማዘንጊያም ፈጠን ብለው «ኡኡቴ ለስሙ ነዋ ያንጠለጠሉት?» በማለት ይጠይቃሉ። አለቃም «ለማንጠልጠሉማ ቡሊ ይበልጠኝ አልነበር» በማለት መለሱ።


በጠማማ ቁና ሁለት ሁለት (1)
(49)አለቃ ምግብ በተልባ በልተው አፋቸውን ሳያብሱ አደባባይ ወጥተዋል። አንዲት የተልባ ቅንጣት ወደ አገጫቸው ተለጥፋ ኖሯለች።አንድ ተጫዋች ወዳጃቸው አለቃ «ዛሬ ተልባ ስንት ስንት ዋለ?» ብሏቸዋል። አለቃም ገብቷቸው ስለነበረ ሰውየው የኔ ብጤ ውልግድግድ ያለ ስለነበረ «በቅፅበት በጠማማ ቁና ሁለት ሁለት ዋለ» አሉት አሉ።


በጠማማ ቁና ሶስት ሶስት (2)
(50)አለቃ ገብረሀና የኢትዮጵያ ዘመናዊ ጥበበ ቀልድ /ኮሚዲ መስራች ሊባሉ ይገባል። አንዳንድ ተቺ ሰው አለ አይደል ዝም ብሎ መተቸት የሚወድ አይነት። አለቃ የበሉት ተልባ አፋቸው ላይ ሳይጠረግ አይቶ «ተልባ ገበያ ላይ እንዴት ዋለ?» ቢላቸው ሰውየው አፉም እግሩም የተጣመመ ስለነበር «በጠማማ ቁና ሶስት ብር ነበር።» አሉት።


አለቃ አለ ዕቃ
(51)አንዴ አለቃ ገብረ ሀና መንደራቸው ካለ ግድግዳ ተጠግተው ሽንታቸውን እየሸኑ ሳለ ,አንድ ጎረቤታቸው አይቷቸው ሰላምታ ሊሰጥ «አለቃ» ቢላቸው እሳቸው «ቆሜ ስሸና እያየህ እንዴት አለቃ (= አለ እቃ ) ትለኛለህ» አሉት ይባላል።


ሰይጣኑ ይውለድህ
(52)አለቃን አንዱ «ምነው ትንቦ ይጠጣሉ?» ቢላቸው። «ብጠጣው ምን አለበት?» አሉት። እሱም «ኧረ የሰይጣን ነው ይባላል። ስለዚህ ነውር ነው!» አላቸው። እሳቸውም ቀበል አድርገው «ሰይጣኑ ይውለድህና ያን ጊዜ ትከሰኛለህ! ለመሆኑ አንተ ለሰይጣኑ ምኑ ነህ?» አሉት ይባላል። (ምንጭ :- ቢልጮ 1948 ከአበበ አይቸህ )


በሌባ ጣትሽ አታሳዪኝ
(53) አለቃ እጓሯቸው ዱባ ተክለዋል። ዱባውም አድጎ ፍሬ ይዟል። ፍሬውም ጎምርቶ (አሽቷል ) እሱንም ጧት ማታ እየተንከባከቡ ይጠብቃሉ። ከጎረቤታቸው አንዲት በሌብነት የሰለጠች ጋለሞታ ነበረች። አንድ ቀን ጧት ወደ ቤተክርስቲያን ሲሄዱ አይታ ቀጥፋ ወሰደችባቸው። ሲመለሱ ዱባቸውን ያጡታል አዝነውና ተናደው ወይ ዱባዬ እያሉ ሲቃትቱ ያቺ አልማጭ ሌባ ከቤት ወጥታ «ምን ሆኑ አለቃ?» አለቻቸው። እሳቸውም «ዱባዬን ጉድ ሆንኩ ተሰረቅሁ» ይላሉ። እሷም ያዘነች በመምሰል ከንፈሯን እየመጠጠች የዱባው ፍሬ የነበረበትን ስፍራ በሌባ ጣታ እያመለከተች «አዎ አለቃ ትላንትና እዚህ ነበር እኔም አይቼዋለሁ» ስትል እሷ እንደሞጨለፈችው አውቀው «ተይው ልጄ በሌባ ጣትሽ አታሳዪኝ» ብለው ስርቆቷን ነገሯት።


አንቺ ባይበላሽ (1)
(54)አለቃ ጠዋት ተነስተው ወጥተው፤ ስራ ውለው ለምሳ ሲመለሱ በጣም እርቧቸው ነበርና ምሳ እስከሚቀርብላቸው ይጠብቃሉ። ማዘንጊያ ሆዬ ለካስ ስራቸውን እየሰሩ ከአይቡም ጎረስ ሲያደርጉ ውለው ነበርና ምሳ ላይ ቸለል ብለዋል። አለቃም «ማዘንጊያ አትበይም» ብለው ቀና ሲሉ አፋቸው ላይ አይብ አይተዋል። «አይ ማዘንጊያ በይ ተይው አንች ባይበላሽ እኔ እበላዋለሁ» አሉ ይባላል።


አንቺ ባይበላሽ (2)
(55)አለቃ አመሽተው እቤት ይመጣሉ ባለቤታቸው ቁጭ ብላ ፈትል ትፈትል ነበር። «እንደምን አመሹ አለቃ?» ትላለች «እኔስ ደህና ይላሉ»። ትንሽ ቆይታ እራት ታቀርባለች እንጀራ በሚጥሚጣ። አለቃም «ነይ ቅረቢ ይሏታል»። «አይ እኔ አልበላም ትላለች»። አለቃም «አይ አንች ባይብ በላሽ እኔ እበላዋለሁ» አሉ።


ቤቴ በየት ዞረህ መጣህ
(56)እንግዲህ እሳቸው አያልቅባቸውም አይደል አንዴ ምን ሆኑ መሰላችሁ። ሚስታቸው ወይዘሮ ማዘንጊያ ነጋ ጠባ እንጀራ በተልባ እያቀረቡ ቢያስቸግሯቸው ጊዜ የተለየ ምግብ አላጣም ይሉና ቅምጣቸው ቤት ብቅ ይላሉ። ውሽማቸውም «ደህና መጡ» ትልና እንጀራ በተልባ ታቀርብላቸዋለች። ከዛ አለቃም በተራቸው ውሽሚት ሳትሰማ ዞር ብለው «ቤቴ በየት ዞረህ ቀደምከኝ ብለው እርፍ»።


መቋሚያዬን አቀብዪኝ
(57)አንድ ቀን አለቃ ቀን ዘመድ ጥየቃ ውለው ሙቀቱ ድብን አድርጓቸው ድክም ብሏቸው ቤት ሲገቡ ባለቤታቸው ወይዘሮ ማዘንጊያ ወጥ እየሰሩ ይደርሳሉ። አሁን ገብተው አረፍ እንዳሉ ባለቤታቸውን መጠባበቅ ጀመሩ የሚበላ ነገር እንዲያቀርቡላቸው ግና ወ /ሮ ማዘንጊያ እየደጋገሙ ወጡን በማማሰያ ሲቀምሱ የታዘቡ አለቃ «ማዘንጊያ እንግዲህ እራታችን እሱ ከሆነ ለእኔም መቋሚያዬን አቀብዪኝ» ብለው እርፍ።


ባዶ ሽሮ
(58)ወራቱ ሁዳዴ ነው ታዲያ አለቃ ሲያስቀድሱ ውለው እቤት ይመለሳሉ። የአለቃን መምጣት ያዩት ማዘንጊያም ምሳ ለማቅረብ ተፍ ተፍ ይላሉ ታዲያ በዚህን ጊዜ አለቃ ከማዘንጊያ ደረት ላይ ተጣብቃ የቀረች አይብ ያያሉ። ትንሽ ቆይቶም ማዘንጊያ ባዶ ሽሮ ወጥ ይዘው ይቀርባሉ። አለቃም «በይ ነያ እንብላ?» ማዘንጊያም መልሰው «አይ እቴ ይቅርብኝ አላሰኘኝም።» አለቃም ማዘንጊያን ምሳቸውን አይብ እንደበሉ ገብቷቸው እንዲህ አሉ አሉ «በሁዳዴ ሽሮ እንዳይጥም አውቃለሁ አንቺ ባይበላሽ እኔ እበላዋለሁ»


ነዪ ብዪ እንጂ
(59)ጾም ነው ሮቡዕ ቀን። አለቃ ጸሎት ከአጥር ግንብ ጎን ሆነው ይደግማሉ እንደገናም ወዴቤት እያሾለቁ ይመለከታሉ። ወይዘሮ ማዘንጊያ ወተት ንጠው ወተቱን አፍልተው አይብ ሠርተው እሱን ጎረስ ጎረስ ጎረስ በጤፍ እንጀራ ያደርጋሉ። አለቃ ይኼንን አይተዋል። ፀሎት አሣርገውወደ ቤት ይገባሉ ከሠዓት ላይ ነው። ለአለቃ ማዘንጊያ ቁርስም ምሣቸውን በማሰብ ምግብ በሽሮ ወጥ ያቀርቡላቸዋል። ይሔኔ አለቃ ማዘንጊያሽ «ነይ ብዪ እንጂ» ይሏቸዋል። ማዘንጊያም «አለቃ ምግብ አልበላ ብሎኛል ይሏቸዋል» ይሄኔ አለቃ «አንቺ ባይበላሽ እኔ እበላዋለሁ» ብለው ብቻቸውን ምሣቸውን በሉ ይባላል።


ገብርኤልና ሚካኤል ተታኮሱ
(60)ወይዘሮ ማዘንጊያ ይፈሱና «ውይ ገብርኤልየ» ይላሉ። ይቆዩና እንደገና ይፈሳሉ «ውይ ሚካኤልየ» ይላሉ ከዛ ድንገት ዞር ሲሉ አለቃ ገብረሀናን በመስኮት ቆመው ያዩዋቸዋል። ድንግጥ ይሉና «እርሶ ደግሞ እዛ ቆመው ምን ያረጋሉ?» ብለው ይጠይቋቸዋል።አለቃ ገብረሀና ደግሞ «እን..ዴ.. ገብርኤልና ሚካኤል ሲታኮሱ እያየሁ ነዋ!» አሏቸው ይባላል።


ለምን ደወልሽው
(61)አንድ ሴት ዉሀ ልትቀዳ ጎንበስ ስትል አንድ ጊዜ ያመልጣትና ድዉ ታደርገዋለች። ዘወር ብላ ስታይ አለቃ ገብረሀና ከኋላዋ ቆመዋል። ከዛም ደንገጥ ብላ «አለቃ ለመሆኑ ሰአት ስንት ሆነ ስትላቸው?» «አይ አንች ካላወቅሽዉ ለምን ደወልሽዉ?» አሏት ይባላል።


ቃታ መፈልቀቂያሽን
(62)ሴትዮዋ ድምጽ ሳይሰማ ማስተንፈስ ፈለጉና በጣታቸው አንድ መቀመጫቸውን ከፈት አድርገው ቢለቁት ሳይሳካላቸው ቀርቶ ዱጥ ቢልባቸው ደንግጠው «ደራን ወጋው» ይሉና ዞር ሲሉ አለቃን ያዩዋቸዋል። ከዛም “አለቃ መቼ መጡ?” ብለው ቢጠይቋቸው «ደራ የተወጋ ጊዜ» ብለው ይመልሱላቸዋል። ሴትዮዋም በመደንገጥ «ምነው ጣቴን በቆረጠው?» ቢሉ አለቃም ቀበል አድርገው «ተይ እንጂ ምነው ቃታ መፈልቀቂያሽን» አሏት አሉ፡፡


ጠረር አድርገሽ ቅጂው
(63)አለቃ አንድ ጊዜ መንደር ጠላ ቤት ይገቡና ሲጠጡ አሳላፊዋ አንዴ እሳቸው ጋር ስትደርስ የተፈጥሮ ነገር ሆኖ ፈስዋ ያመልጣትና ጠርር ታድርገዋለች እየቀዳች። ይህን የሰሙ አለቃ አንድ ጊዜ እሳቸው ጋር መጥታ «አለቃ ጠላ ልጨምርልዎት እንዴ?» ስትላቸው። «አዎዋ እስቲ እንደ ቅድሙ ጠረረ አድርገሽ ቅጂው» አሉ ይባላል።


አንድማ ግዙ
(64)አለቃ ገብረሀና መሸት ሲል ጠላ ቤት ተቀምጠው ሲጠጡ ቆዩና ሽንት ለመክፈል በጓሮው በኩል ወጣ ብለው በሚሸኑበት ጊዜ ፈሳቸው ያመልጣቸውና ጡጥ ያደርጋሉ። ሰው ሰምቶ ይሆን ብለው ትንሽ ዞር ብለው ሲመለከቱ ኮማሪትዋም ትንሽ ራቅ ብላ እቃ እየፈለገች ኖራ ሰምታ ይሆናል ብለው በመስጋት አህያ እንደሚያባርሩ በመምሰል «ዙር !! ዙር !!» ብለው ሲጣሩ ሴትዮዋ ሰምታ «ኧረ! እኛ አህያ የለንም» ስትል አለቃ መልስ አይጠፋቸውም አይደል «አንድማ ግዙ» አሉ ይባላል።



በጠርር ሄጄ በታህሳሥሥ
(65)አንድ ጊዜ አለቃ በመንገድ ላይ ከወዳጃቸው ጋር ሲሔዱ ወዳጃቸው ፈሱን መፍሳቱን ሰምተው ኖሮ ሰለነበር እንዴት እንደሚናገሩ እያስቡ ሳለ ድንገት ሰውየው «መቼ ነው ከከተማ የመጡት» ቢላቸው «በጠርርርር ....... ሄጄ በታህሳስስ .... ተመለስኩ» አሉ ይባላል። ሰውየን ማሰቀየም አልፈልጉም ማለት ይሆን?


መልግጌ አባስኩት
(66)አለቃ ለቅሶ ሂደው ራት ከተበላ በኋላ ተጎዝጉዞ ከለቀስተኛ ጋር በመደዳ ይተኛሉ። ትንሽ ቆይቶ ፈሳቸው ይመጣባቸውና ቀስ ብለው ያለ ድምጽ ሊፈሱ አስበው ቂጣቸውን በጃቸው ከፍተው ቢለቁት ጠርር ብሎ ያሳፍራቸዋል። አለቃም አዝነው «አዬ መልግጌ አባስኩት» አሉ ይባላል።


ድንቼ
(67)አንዲት አጠር ደልደል ያለች ደባካ መሳይ የኣለቃ ገብረሃና ጎረቤት ደግሞ «አባ ሰው ሁሉ ድንቼ የኔ ድንች እያለ ያቆላምጠኛል» ብትላቸው «አዮ ሞኝት እውነት መስሎሽ ነው?ድንቼ ድንቼ የሚሉሽ ሊልጡሽ እንጂ ነው» አሏት።


በነካ አፍህ
(68)አለቃ ገብረሀና ከአንዱ ባለሱቅ ስውየ ጋር ማእድ ተቀምጠው ከተመገቡ በኋላ ስውየው የበላበትን እጁን ሲልስ አይተው ኖሮ «ወንድም በነካ አፍህ» ብለው እጃቸውን መቀሰራቸው ይነገራል።


ተኖረና ተሞተ
(69)አንዲት እድሜ ልኩዋን በድህነት የኖረች አሮጊት በነ አለቃ ገብረሀና ሰፈር ውስጥ ታርፍና ሰው ለቀብር ጉድ ጉድ ሲልና ሲሯሯጥ ሲጣደፍ አለቃ በዚያው መንገድ ሲያልፉ “ምንድን ነው እጅብ እጅቡ” ብለው ይጠይቃሉ። “እንዴ አለቃ አልሰሙም እንዴ ?”፥ “ምኑን?”፥ “ያቺ ደሀ አሮጊት መሞቷን?”። አለቃም ቀጠል ያደርጉና “አሄሄ ተኖረና ተሞተ?” ብለው ተናገሩ። በህይወትም እያለች የቁም ሙት ሞታለች ያም ኑሮ ሆኖ ሞት ለሷም መጣባት ወይ እንደማለት ነው።


መሞትዎት ነው
(70)አባ ገብርሀና የተዎለዱትና አርጅተው የሞቱት በጎንደር ክ /ሀ , ፎገራ ወረዳ ናበጋ ጊዮርጊስ የሚባል ገጠር ነበር። ክርስቶስ ሰምራ እየተባለ የሚታወቀው አካባቢ ማለት ነው። እናም ሰው መቼም ኑሮ ኑሮ መሞት አይቀርምና እሳቸውም ነፍሳቸው ልትወጣ እየተንፈራገጡ ሳለ (ሊሞቱ ማለት ነው) አንድ ከጎናቸው ተቀመጦ ጣረ ሞታቸውን ሲከታተል የነበረ ሽማግሌ አለቃን ጠርቶ «በቃ መሞትዎት ነው?» ብሎ ሲጠይቃቼው፣ «የግሚት ልጅ ታድያ ቆዳ እያለፋሁ መሰለህ» ብለውት እርፍ አሉ ይባላል።


የአለቃ የልጅ ልጅ
(71)ነገሩ የሆነው ፎገራ ውስጥ ሲሆን በደርግ ዘመን ነው። ካድሬው ህዝቡን ሰብስቦ ስለ መንደር ምስረታ አስፈላጊነት ሲያብራራ «በመንደር ከሰፈራችሁ ውሃና መብራት በየቤታችሁ ይገባላችኋል» እያለ ከቀሰቀሰ በኋላ የህዝቡም ተቃውሞ አዳማጭ ሳያገኝ ሰፈሩ ሜዳ ላይ ተሰርቶ ሕዝብ ሰፈረ። ክረምት ሲመጣም ጣና ሐይቅ እንደተለመደው የፎገራን ሜዳ ቤቴ ብሎ ሲያጥለቀልቀው ህዝቡ ወደ በአካባቢው ከተሞች ተሰደደ። በዛን ወቅት የአለቃን የልጅ ልጅ ጋዜጠኛ አግኝቶ ስለ ሁኔታው ሲያነጋግረው «ያው በካድሬው እንደተነገረን ውሃው በየቤታችን ገብቷል መብራቱ ብቻ ነው የቀረው» ብሎ አስተያየቱን ሰጠ።