lunedì

ግጥም ብጤ


ፖሞዶሮና ፓስታ ቅርጭም አደርግና
አንድ ጣሳ ቢራ ጭልጥ አደርግና
ተመስገን እላለሁ ኑሮ ይባልና።
.
ስፐር ማርኬት ቡስጣ ስሸከም እውልና
ስህን ሬስቶራንት ሳጥብ አመሽና
በኩራት እተኛለሁ ነገም ሌላ አለና።
.
ከቀናኝ ፊሶ ሥራ አገኝና
ወይም ሽማግሌ ጠባቂ እሆንና
ትላንትን እደግማለሁ ዛሬም እንደገና።
.
ጊዜው ሲገሰግስ ዘመኑም ሲረዝም
ሥራዬን ለዘመድ ለወዳጅ አልነግርም
እርዳኝ ባይ ጠያቂ በጭራሽ አልወድም
አገር ግባ የሚለኝ ምክርም አልፈቅድም።
.
ባገር ያለ ሁሉ ከንቱ ይመስለኛል
የፈረንጁ ነገር ክሱም ይደንቀኛል።
.
እንደመልካም ነገር ተሰደድኩ እላለሁ
ግን ክብር ያለሀገር እንደሌለ አውቃለሁ።
.
ዛሬ አያችሁ እንጂ ሳድር በሰው ሀገር
ከዋሉ ካደሩ ለእኔም አለኝ ምድር።
.
ሰው ያለሀገሩ ቢበላ መቅመቆ
መከበር አለበት ሰውነቱ ታውቆ።
.
ሰው ክለሀግሩማ ካለቦታው
ብሳና ይሆናል ሸንኮራ አገዳው
መህይም ይመስላል ብዙ እውቀት ያለው።
.
ካገሩ የወጣ ሀገሩ እስኪመለስ
ኑሮውን ይገፋል ክብሩን በማስገሰስ።

domenica

”TROPPI MASSACRI MAI RACCONTATI”


Lo storico Angelo Del Bocca
.

"LE STRAGI FASCISTE IN ETIOPIA RIMOSSE PER VOLONTA’ POLITICA"
Intervista allo storico Del Boca dopo le rivelazioni di Repubblica:”Troppi massacri mai raccontati”
La Repubblica 23 maggio 2006 (pagina 29)

ANAIS GINORI

UNA strage dimenticata che riaffiora insieme agli orrori commessi dall’esercito italiano in Etiopia. La foiba assassina scoperta da uno studioso di Torino, Matteo Dominioni, e raccontata ieri da Repubblica, rilancia la polemica sui massacri commessi durante l’avventura colonialista di Mussolini.
Trail 9 e l’11 aprile 1939° Debra Brehan, 100 chilometri a nord di Addis Abeba, furono fucilati e avvelenati con i gas centinaia di guerriglieri che si erano rifugiati in una grotta insieme alle loro famiglie. Donne, vecchi, bambini. Mille morti, almeno. “ Ed è soltanto uno dei tantissimi massacri che devono essere pienamente indagati” racconta Angelo Del Boca, il maggior storico del colonialismo italiano nel suo ultimo libro, Italiani, brava gente?, ha invitato l’Italia repubblicana ad ammettere i crimini di quegli anni.
Nel massacro di Debra Brehan furono usati contro la popolazione gas e persino lanciafiamme. Come spiegare una tale ferocia?
“Alla fine del 1938 la resistenza abissina era ancora fortissima e Mussolini era molto scontento di come stavano andando le cose nell’Africa Orientale. Il Duce voleva una repressione ancora più violenta. I gas iprite e fosgene furono usati in maniera continuativa durante la guerra”.
Perché settant’annni dopo la nostra memoria rimuove ancora episodi come questo?
“ La mia ricerca del 1966 sui massacri in Etisia fu accolta in maniera disastrosa da gran parte del mondo politico. Non solo dai fascisti o neo-fascisti ma anche degli ambienti conservatori per cui certe cose non si possono dire perché siamo, appunto brava gente”.
Adesso siamo pronti a riscrivere la storia?
“ E’ un lento cammino. Fino agli anni 80 nei libri di scuola si parlava ancora di “battaglia di civilizzazione”. Adesso la storiografia è più moderata ma certo non si fanno studiare ai ragazzi stermini come questo.”
E invece ci sarebbero altri eccidi da raccontare.
“ Deportazioni di massa, bombardamenti con bombe di iprite, campi di concentramento, rappresaglie indiscriminate, stragi di civili, confisca di beni e terreni. Uno degli episodi più gravi fu il massacro della città sante di Debre Libanos dove nel maggio 1837 furono uccise quasi duemila persone, in gran parte preti, sacerdoti e pellegrini”.
Pensa che il governo etiope dovrebbe chiedere un risarcimento?
“ Credo sia impossibile. Alla fine degli anni Cinquanta, quando sono state ristabilite le relazioni tra l’Italia e l’Etiopia, il nostro governo costruì una diga e versò dei soldi come risarcimento. Non era cert una somma che pagava i 300mila morti della guerra ma fu comunque un atto simbolico”.
Continuerà ad indagare su questi crimini della colonizzazione?
“ Per anni l’archivio del Ministero degli Esteri è stato inaccessibile. Soltanto quando al centro di documentazione è arrivato Enrico Serra, un partigiano come me, sono riuscito a fare le mie ricerche. Lo Stato rende difficile il lavoro d’indagine sul colonialismo, ci sono ancora migliaia di falconi intonsi proibiti agli studiosi. E chissà quante cose potremmo scoprire se solo ci fosse la volontà di far luce sul nostro passato”.
"GLI STUDIOSI FATICANO AD ACCEDERE AGLI ARCHIVI PUBBLICI. NEI LIBRI DI SCUOLA NON SI RACCONTANO GLI ECCIDI."

sabato

ከአውሮፓ ስለሚባረሩት ኢትዮጲያውያን/ት የሬዲዮ ቃለ ምልልስ ለማዳመጥ


..... በአውሮፓ ስላሉ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን በተመለከተ ከአቶ ምስጢረ ኃይለሥላሴ ጋር የተደረገ ቃለምልልስ
በካናዳ ቫንኮቨር ከተማ የሚገኘው "ራዲዮ ኢትዮጵያ" በአውሮፓ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ላይ እየደረሰ ስላለው ችግር፣ መንገላታትና አስገድዶ ከአገር ማስወጣትን በተመለከተ ቃለምልልስ አድርጎላቸዋል።
..... ቃለምልልሱ የተደረገው ነኀሴ 15 ቀን 1997 ዓ.ም. (ኦገስት 21 ቀን 2005 እ.ኤ.አ.) ሲሆን፣ ቃለምልልሱን ያደረጉላቸው ጋዜጠኛ አትክልት አሰፋ እና ጋዜጠኛ ቶማስ ተስፋ ናቸው። ራዲዮ ጣቢያው ዘወትር እሁድ በካናዳ፣ ቫንኮቨር ከተማ ሰዓት አቆጣጠር ከጠዋቱ 3 ሰዓት (9ፒ.ኤም. ፓሲፊክ ታይም) ጀምሮ ለአንድ ሰዓት የስርጭት ፕሮግራም ሲኖረው በቀጥታ በዚህ በሚከተለው የድኅረ-ገጽ አድራሻ ላይ ይደመጣል። ስለዚህም ይጫኑትና ያዳምጡ

mercoledì

የነገው የውጪ ዜጎች ዕጣ


የዛሬ 10 ዓመት በፊት ክነበረው ጋር በማወድደር በመጨረሻዎቹ 5 ዓመታት ውስጥ በርካታ ስደተኞች ወደ አውሮፓ ሲፈልሱ ታይቷል። ይኸው ጉዳይ የፖለቲከኞችና የህዝቡ መነጋገሪያ አጀንዳ ከሆነ ሰነበቷል። በአንድ በኩል የውጪ ዜጎች የስራ ዕድል ተሻሚ ናቸው ሲባል በሌላ ወገን ደግሞ ወደፊት የአውሮፓ ሰራተኛ ህዝብ ቁጥር እየቀነሰ ስለሚሄድ የውጭ ዜጎች ይህን ክፍተት ይሞላሉና ፍልሰቱ መቀጠል አለበት የሚል ክርክርም ይነሳል። በዚህም ምክንያት አሁን በአውሮፓ ያለው ሁኔታ ለስደተኞች ምንም የሚያበረታታ አይደለም።
ብዙዎች በየብስ ሆነ ባባህር ድንበር አቋርጠው ወደ አውሮፓ ለመግባት በሚያደርጉት ሙከራ መንገድ ላይ ህይወትን እስከማሳለፍ ደረጃ የሚደርሱበት ሁኔታ እየጨመረ መጥቷል። በተለይም በቀይ ባህር አድርገው ወደ ልዩ ልዩ የአውሮፓ አገራት ለመግባት በየስደተኞች ሰፈር የሚጠባበቁ ከቀድሞው የባሰ ፈተና ነው የሚጠብቃቸው። ምክንያቱም ወደ አውሮፓ የመሻገሪያው ድንበር እጅግ ከፍ ብሎ እየታጠረ በመሆኑና እዚህም በሚገኙት ላይ ከዚህ ቀደም ልል የነበረው ህግ እየጠበቀ በመምጣቱ ነው።
በተለያዩ ሀገሮች ያሉ ፖለቲከኞች በስደተኛ ላይ የያዙት አቅዋም የተለያየ በመሆኑ ከብዙ አቅጣጫ ትችት እየተሰነዘረበት ነው። በእያንዳንዱ የአውሮፓ ሀገር ውጭ ዜጎች ፍልሰት ህግ ሁሉም እኩልና አንድ ወጥ የሆነ ህግ እንዲኖራቸው ያስፈልጋል። በተለይ ሽብርተኞች በዩናይትድስቴትስ ላይ ካደረሱት እ.ኤ.አ የመስከረም 11 2001 ጥቃት ጋር አያይዘው የአውሮፓ ሀገሮች በውጭ ዜጎች ላይ ቁጥጥሩን በማጥበቃቸው ብዙዎቹ የተለያዩ ህጎችና ድንጋጌዎችን ስላወጡ ብዙ ተተችቶበታል።
ለምሳሌ አብዛኛዎቹ መሪዎችና ፖለቲከኞች ስደተኞችን እየመረጡ የማስገባቱን መርህ ደጋፊዎች ናቸው። ከነዚህም አንዱ የፈረንሳይ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ኒኮላሳ ሳርኮዚ ናቸው። ኒኮላስ በአንድ ወቅት “ዕርዳታ ፈላጊ ስደተኛ አንፈልግም እኛ የምንፈልገው ለኛ የሚስማሙንን ነው። ይህም ማለት በአስተማማኝ ሁኔታ ለፈረንሳይ ዕድገት አስተዋፅኦ ሊያበረክቱ የሚችሉትን ነው በተለይ የምንመርጠው“ ብለው ነበር። ይህ አባባል በሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ዘንድ ተቀባይነት የለውም።
በአውሮፓ ከጥቂት ዓመታት በኋላ ብዙሀኑ በዕድሜ እየገፉ ስለሚሄድ የውጭ ዜጋ ወደ አውሮፓ እንዳይገባ ገደብ ይጣል መባሉ የትም እንደማያደርስ ነው የተገመተው። አሁን ባለው ግምት መሰረት እ.አ.አ. እስከ ሁለት ሺህ አስራ አምስት ከአውሮፓ ህዝብ አንድ ሶስተኛው ዕድሜው ከሀምሳ ዓመት በላይ እንደሚሆን ነው የተገለፀው። እናም ያኔ ስደተኞች ስራ ይሻሙናል የሚል ስጋት ቀርቶ ሳይወዱ በግድ ስደተኞችን መሻታቸው አይቀርም። ይሁንና ተጨባጩ ሁኔታ ብናጤነው የህብረተሰቡ ስጋት ምኑ ላይ እንደሆነ ለመለየት ይቸግራል።
ብዙዎቹ ስደተኞች ህጋዊ ባለመሆናቸው የስራ ዕድል የላቸውም። የስራ ሽሚያውም አይመለከታቸውም። ስራ ለማግኘት ብዙ ነገሮችን ማሟላት ያስፈልጋል። ብዙ እስያውያን ሴቶች ህፃናትን የሚንከባከቡ፣ የህፃናት ሞግዚት ሆነው የሚሰሩ፣ በቤት ውስጥ ስራ የተሰማሩ፣ በየመዝናኛ ስፍራዎች ሲያገለግሉ ነው የምናያቸው።
ያለንበት ዘመን ዓለም ዓቀፋዊ የኢኮኖሚ ትስስር ዘመን ስለሆነና ጊዜው የነፃ ገበያ ወቅት በመሆኑ ህዝቦች ከአንዱ አገር ወደ ሌላው ለስራ መሰደዳቸው ጤነኛ አካሄድ ነው። አውሮፓውያን መሪዎችና ፖለቲከኞች ስደተኛውን እንደ አደጋ ሳይሆን ጠቃሚ የልማት አስተዋፅኦ ሊያበረክት የሚችል ሀይል አድርገው መመልከትና እንዲህም የውጭ ዜጎች ወደ አውሮፓ የሚገቡበትን ስርአት በደንብ ማስተካከል ይገባቸዋል።