venerdì

ከጣሊያን መንግስት የተሰጠ የነፃ እድል ትምህርት

15/04/2008
ከዶ/ር ዘለቀ እሬሶ
የጣሊያን መንግስት መጪዉን የትምህርት ዘመን ማለትም ከሰፕቴምበር 2008 እስከ ኦክቶበር 2009 ያለዉን የትምህርት አመት አስመልክቶ የዉጭ ሀገር ዜጎችን አወዳድሮ ለአሸናፊዎቹ የነፃ እድል ትምህርት ማለትም እስኮላርሺፕ ለመስጠት አቅዶ በነበረዉ ፕላን መሰረት ሰሞኑን በአገሪቱ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል የነፃ እድል ትምህርት ማስታወቂያ ማዉጣቱ ታዉቆአል::
ለጊዜዉ የነፃ እድል ትምህርቱ ለስንት ተማሪዎች ሊሰጥ እንደታቀደና የእስኮላርሺፑ ትክክለኛ ቁጥር ስንት እንደሆነ በግልፅ የተሰጠ ዝርዝር መግለጫ ባይኖርም እድሉ ሁሉንም የትምህርት ዘርፎች እንደሚያጠቃልል ከወጣዉ ማስታወቂያ መረዳት ተችሏል::
መወዳደር የሚፈልግ ሁሉ በቀጥታ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን ወይንም በየአቅራቢያዉ ያሉትን የጣሊያን አምባሲ ጽ/ቤት በቀጥታ በመጠየቅ አስፈላጊዉን መልስ ማግኘት ይችላል::

ለመወዳደር ምን ያስፈልጋል?
- የትምህርት ደረጃን የሚገልፅ ማስረጃ;
- እድሜዉ ከ 35 አመት በላይ ያልሆነ

የትምህርት ዘርፎች
- የአጭር ጊዜ የጣሊያንኛ ቋንቋ ትምህርት;
- የተለያዩ የዩኒቨርስቲ አጫጭር የሙያ ነክ ኮርሶች;
- የተለያዩ መካከለኛ የሙያ ማሻሻያ ኮርሶች;
- በተለያዩ መስኮች የዲግሪ ትምህርት;
- በተለያዩ መስኮች ከመጀመሪያ ዲግሪ ቀጥሎ ያሉትን ትምህርቶች ማለትም የፖስት ግራጁዌት እስከ ዶክትሬት ድረስ;
- ባህላዊና ሙዚቃዊ አጫጭርና የረጅም ጊዜ ትምህርቶች;
- እና የመሳሰሉትን ያጠቃልላል::
መልካም እድል ለሁላችሁ

Nessun commento: