venerdì

ንዑስ ኮሚቴዎች


1 - የመጽሔት እንዴት ሰነበተች
የኢትዮጲያ ባህላዊ ማህበር ቤኤሚሊያ ሮማኛ በ2001 ዓም በየሁለት ወሩ አዘጋጅቶ የሚወጣ መጽሔት ማተምና ለአባላት ማደላደል ጀምሮ የመጨረሻውንና ስድስተኛውን ቁጥር አውጥቶ እንደቆመ ቀረ፡፡ ከዚህም በኋላ ምን ላይ እንደደረሰ ማወቅ ለሚሹት የግድ መልስ መስጠት ተገቢ ነው፡፡
.
ብዙኃን ተካፍለው አስተዋጽዖ ያደርጋሉ የሚል እምነት ስለነበረን ... ለሕትመት የሚደረገውን ወጪና ለስርጭት ወደፊት እራሱን የሚችል ስለሆነ ለመጀመር የግድ የተወሰነ ወጪ ስለሚኖረው ከማሕበሩ የተወሰነ ገንዘብ ወስዶ ሥራው ሊጀመር ይቻላል በሚል ተወያይተን ወሰንን፡፡ በመጀመሪያም ይህንን ለማድረግ ህጋዊ የሆነ ንዑስ ኮሚቴ (redazione) እንዲኖረው አደረግን። የኅትመት ኃላፊነቱ የተወሰነ እንዲሆን ብለን በቦሎኛ ፍርድ ቤት አዋጅ ቁጥር 7089 - 08/02/2001 በጋዜጦች ... በአልቦ ሕጋዊነት እንዲኖረው አደረግን፡፡ ይህንንም ለማድረግ ገንዘብ ወጪ ተደረገ፡፡ ከዚያም አንባቢያን በተወሰነ ክፍያቸው በconto corrente postale (Bolettino) አማካኝነት እየከፈሉ እንዲደርሳቸው ለማድረግ ሌላ ወጪ ተደረገ፡፡ የመጀመሪያዎቹን 3 እትሞች (ቁጥር 1/2/3/)ን ሁሉም እንዲያውቁልን ብለን በነፃ ካደላደልን በኋላ የመጨረሻዎቹን 3 እትሞች (ቁጥር 4/5/6)ን መላክ ስንጀምር እስከ መቶ ለሚደርሱ ክተላከላቸው ውስጥ በቁጥር 12 የሚደርሱ አባላት ብቻ abbonati ሆኑ፡፡ ለመጽሔቷ እድምተኛ የሚሆኑት በቁጥር ይጨምራሉ በሚል እምነት አሳትመን የምናወጣው በቁጥር አስከመቶ ይደርስ ስለነበረና ያም ብዙ ወጪ ስለነበረበት መጽሔቷ የተላከላቸውና የደረሳቸው ምንም አይነት ክፍያ ባለማድረጋቸው የሕትመቷ መቋረጥ አንዱ ምክንያት ሆነ፡፡ ዓመታዊውን ክፍያ አጠናቀው የከፈሉት 12ቱ .... ደግሞ የደረሳቸው ሦስት እትም ብቻ ነው፡፡ .... (ይቀጥላል ... )
.
ዋናው የመጽሔት ዓላማም ከብዙ በጥቂቱ ከዚህ በታች የተዘገቡት ነበሩ፡፡
* የመወያያ መድረክ በመሆን ልጆቻችንና ወንድሞቻቸን እህቶቻችን ለዚህ የውጪ ሀገር ኑሮ ለማዘጋጀት
* በውጪ ሀገር ስንኖር ሊያጋጥሙ ን በሚችሉ የጋራ ችግሮች ላይ በመተባበርና በመረዳዳት ህጋዊ በሆነ መንገድ መፍታት እንዲቻል
* በምንኖርበት በጣሊያን ሀገር ህግና ደንብ መሠረት በዜጎች እኩልነት መርህ ላይ በመመሥረት የኩልነት መብቱን የሚጠበቅበትን መንገድ መዘርጋት እንዲቻል
* የኢትዮጲያን የባህል፣ ልምድ፣ የኑሮ ሁኔታና የመሳሰሉትን በምንኖርበት አካባቢ ማሳወቅ እንዲቻል
* ከአካባቢያችን ውጪ በተለያዩ ሀገሮች ከሚኖሩ አኢትዮጲያዊያንና ሌሎች የውጪ ሀገር ዜጎች ጋር ሃሳብ ለሃሳብ የመለዋወጥ ግንኙነት እንዲኖር
* የታሪክ ዘገባዎችን በአስተናጋጁ ሀገር ቋንቋ፣ እንዲሁም የአማርኛ ፅሁፎችን ቅኔዎችን፣ ግጥሞችንና፣ ማንኛቸውንም ቁም ነገር አዘልና ቀልዶችን ወዘተ ... ለአንባቢያን ለማቅረብ
* የኪነጥበብ፣ የስፖርት ችሎታቸውን እንዲያዳብሩና ለአደባባይ እንዲበቁ ማገዝ ...እንዲሁም ሌሎችም ... ... ... (ይቀጥላል)
.
2 - የእርዳታ ማሰባሰቢያ ኮሚቴ
በአለፈው 2003 ዓም በሃገራችን ሰፊና አሰቃቂ ለነበረው በረሀብ የተጋለጡትን ወገኖች ለመርዳት እዚህ ያለነውን አሰባስበን ግዴታችንን ለመወጣት የእርዳታ ማሰባሰብ ፕሮግራም ተደርጎ ነበር፡፡ እንግዲህ በወቅቱ ከነበረን ውይይትና ወገናችንን ለመርዳት ካለን ሙሉ ፍላጎት በመነሳት “ለወገኖቻችን እንድረስላቸው” በሚል ግብታዊ (spontaneous) በሆነ መንገድ ተሰባስበን ገንዘብ ማዋጣታችንና በማህበሩም አማካይነት የሙዚቃ ምሽት ተደርጎ ገንዘብ ማሰባሰባችን የታወቀ ነው፡፡ ይህንን የእርዳታ ማሰባሰብ ሁኔታ ለማካሄድ በቁጥር 3 አባላት የያዘ ጊዜያዊ የእርዳታ አስተባባሪ መቋቋሙ ይታወሳል፡፡ የፈጸማቸውን ጉዳዮች በሚመለከት ደግሞ በተደረግውን ከፍተኛ ትብብርና በሚያኮራ መንገድ ደምድሟል፡፡ ነገር ገን ከሚመለከተው ክፍል የምስጋናም ሆነየደርሶናል ዜና ማንኛችንም አልሰማንም፡፡ ይህንንም በሚመለከት ጉዳይ ንዑስ ኮሚቴው የሚያቀርባቸውን መግለጫዎችን ለመስማት ብዙሃን አባላቶች የሚሹት ሆኖ በመገኘቱ.. ማብራሪያዎችን ቢሰጥበት ጥሩ ሆኖ ይገኛል፡፡ ወደፊት ይህ ንዑስ ኮሚቴ ሌሎች ተመሳሳይና የተቀደሱ ሁኔታዎችን ለማድረግ ሃሳብ ከአላቸው ... (ይቀጥላል ...)

Nessun commento: