lunedì

የኢትዮጲያ ባህላዊ ማህበር በኤሚሊያ ሮማኛ


ይህ ማህበር የተመሠረተው እ.ኤ.አ. በ1994 ዓም ነው፡፡ አመሰራረቱና ድርጅታዊ ቅርፁ በሚገባ የተዋቀረና የተማከለ እንደነበረ ከማህበሩ ጋር ቅርበት ያለው ሁሉ የሚያውቀው ነው:: ዓላማዎቹ በኤሚሊያ ሮማኛ የሚኖሩትን ኢትዮጵያውያን በማህበራዊና በባህላዊ ነክ ጉዳዮች አማካኝነት መሰባሰብንና መቀራረብን ለመፍጠር ነበር። በተመሠረተ በመጀመሪያዎቹ ዓመታት ውስጥ ለዚህ ማህበር መጠናከር በርከት ያሉ ግለሰቦች ጥረት ያደርጉ ነበር። ነገር ግን በተግባር ለመተርጎም የግለሰቦች መልካም ፈቃድንና የህብረት ስራን የሚጠይቅ ስለነበር ከዚህም በላይ በተወሰኑ ሥራዎች ላይ የተባባሪዎች ቁጥር በማነሱ የተጠበቀውን ውጤት አላገኘም። በሥራ ክፍፍል ተደርጎ ሁሉም የድርሻውን ቢያደርግና ትብብር ቢያገኝ ውጤት ይኖረው ነበር ለማለት ነው፡፡ ... ይቀጥላል ........

.
የመጨረሻው የማዕከላዊ ኮሚቴ ምርጫ በተካሄደበት ጊዜ በቁጥር 9 የሚሆኑ አባላት ተመርጠው ነበር። ከእነዚህም ውስጥ ብዙኃኑ በማህበሩ የሥራ አስኪያጅነት አባላት የቆዩ ነበሩ። በአሁኑ ጊዜ በማዕከላዊ ኮሚቴ ውስጥ የምንገኘው ከዚህ በታች ስማችን የተቀስነው ነን፡፡
1. ወ/ሮ ጥሩነሽ ----------------- ሊቀመንበር
2. አቶ ሴባስቲያኖ ባርቶሎትታ ---------- ምክትል ሊቀመንበር
3. አቶ አብርሃም ዘውዴ -------------------- ፀሃፊ
4. ወ/ት ሙሉመቤት ----------------- ቴሶሪየሪ
5. አቶ ታደለ እጅጉ ---------------------- አባል
6. ወ/ሮ መቅደስ ---------- ባህልና ሕዝብ ግንኙነት
7. አቶ ደረጀ አባተ --------------------- አባል
8. አቶ ማርኮ ቤሊስትሪ ----------- ባህልና ሕዝብ ግንኙነት
9. ----- .....................
... (ይቀጥላል) ........
.
በ29-01-2005 ...
ሶስት ሆነን (ሙሉመቤት፣ አብራሃም፣ መቅደስ) በአጋጣሚ ምክንያት ስለ ስማህበሩ አንስተን ጭውውት ከፍተን ...
" በአለፈው ዓመት ውስጥ የተደረገ ስብሰባና የተሰራ ነገር የለም፡፡ የጉዳዩ ባለቤቶች ስለሆንን እጃችንን አጣጥፈን እያወራን ብቻ መቀመጡ ከሞራልና ከስነምግባር አንጻር አሳፋሪ አይደለም ወይ? ለምን የአቅማችንን እንኳን አንድ ነገር አናደርግም? ሃላፊነትን ይዘን የሙጢኝ ለማለት የምንፈልግ ይመስልብናል፡፡ እኛም ብንሆን በራሳችን መካከል ለውጥን የምንሻ ስለሆንን አስፈላጊ ከሆነ አዲሶች እንዲተኩበት በማድረግ ተከታዮችም ልምድ ማካበት እንዲኖራቸው ማድረግም አለብን " ...
በማለት እራሳችን እየተቸን እና እየተወቃቀስን በሶስታችንም በኩል የሚንጸባረቅ አንድ የውሳኔ ሀሳብ ወሰንን፡፡ ምንም እንኳን ህጋዊ የማዕከል ስብሰባ ባይሆንም (ከስራ አስኪያጅ ኮሚቴ በቁጥር ከግማሽ በታች ስለነበርን) አጋጣሚው ላይ ያልነበሩት የኮሚቴው አባላት በሙሉ በሀሳቡ የሚስማሙ መሆኑን ስላወቅን ሌላ ህጋዊ ስብሰባ ተጠርቶ አንድ ውሳኔ ለማድረግ ወሰንን፡፡
.
በዚሁ ዕለት ከተነሱት ነጥቦች መካከል የሚከተሉት ነበሩ...
ማህበሩ ሙሉ ሥራውን እንዲጀምር ከተፈለገ ከሁሉም በፊት ግን መደረግ ያለበት በአሁኑ ጊዜ የሚገኝበትን ተጨባጭ ሁኔታ በመነጋገርና በመመርመር የሚፈለገውን እርምጃ መውሰድና መፍትሄ ሃሳብ መገኘት አለበት፡፡ ስለዚህም ...
1- ከማህበሩ አባላት ውስጥ ግዴታቸውን የሚወጡት ጥቂቶቹ ናቸው፡፡ በስራ አስኪያጅ ኮሚቴው ውስጥም ትንሽም እንቅስቃሴ ቢሆን የሚከናወነው በተወሰኑ አባላቶች ብቻ ስለሆነ ሃላፊነትና የስራ ጭነት አስከትሏል፡፡ ከላይ እንድተጠቀሰው ይህም ሊፈጠር የቻለው ከማህበሩ ኣባላትም ቢሆን ምንም አይነት ትብብርና እንቅስቃሴ ስለማያገኙ ነው፡፡ ስለዚህም ከልብ በመስራት ላይ የነበሩት የኮሚቴው አባላት የማህበሩን እንቅስቃሴና የስራ ዘርፍ ለመሸፈን የሰው ሃይል ስለሚያስፈልጋቸው ይህንንም ሃይል መጨመርና ማጠናከር አስፈላጊ ነው፡፡ በአጠቃላይ ከአባላት ትብብርና የስራ ተሳትፎ መኖር በስራ አስኪያጅ ኮሚቴው ላይ የስራ መደራረብ እንዳይፈጠርበት ስለሚረዳ ...
2- በተለያዩ ምክንያት አገልግሎት ለመስጠትም ሆነ ስብሰባዎች ላይ ለመገኘት የማይችሉ የኮሚቴዎች አባላቶች ማለትም በጊዜ እጥረት፣ በሥራ፣ በቤተሰብ፣ የመኖሪያ አድራሻቸው ሩቅ ለሆኑም ሆነ በአዳዲስ ተመራጮች መተካት ስለሚያስፈልግ ...
3- በአሁኑ ጊዜ የማህበሩ ሊቀመንበር በተወሰኑ ምክንያቶች ሃላፊነቱንና ሥራውን ማካሄድ ስለማይችሉና በፍቃዳቸው ቦታውን መልቀቅ ስለሚፈልጉ ሌላ ሰው እንዲተካበት ምርጫ ማካሄድ ግድ ስለሆነ ...
4- በማዕከሉ አመራር የአባላት ቁጥር የጎደለ በመሆኑ ያሉት ክፍት ቦታዎችን የግድ መሸፈንና መመሟላት ስላለበት ማስመረጥ አስፈላጊ በመሆኑ ...
5- "ማህበሩን ለማራመድ አንዳንዱን የአመራር ቦታ በአዳዲስ ተመራጮች ይተኩበት" የሚል አሳብም ስለቀረበ... ወዘተ ...
.
እነዚህንና የመሳሰሉትን ላይ በመነጋገር ለስራችንን አቅጣጫ የሚያስይዙ አንዳንድ እቅዶችን ነድፈን በማውጣት በአጀንዳ ይዞ ምክር ለማድረግ ወሰንን፡፡ ከእነዚህም እቅድ መካከል በተቻለ መጠን ከተለያዩ አቅጣጫወች ሃሳቦችን እንዴት ለማግኘት እንደሚቻል ነበር፡፡ በዚህም ምክንያት ጥሩ ሃሳብ ሊያመነጩ ይችላሉ፣ ቅን የሆነም ሃሳብ ይኖራቸዋል፣ የማህበሩ መሥራቾችም ስለሆኑ በማህበሩ ውስጥ በአሁኑ ጊዜ ስላለው ተጨባጭ ሁኔታ እንዲገነዘቡልን ይረዳናል ብለን ያመንባቸውን እንግዶች የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ ላይ ጠርቶ ለማነጋገር ወሰነ፡፡
.
ፈቃደኛ የሆኑትን እንግዶች በመጋበዝ ያደረግናቸው ተከታታይ 3 ስብሰባዎችና የተወያየንባቸው አጀንዳዎች በከፊል
- 05/02/2005 (ወ/ት ሙሉመቤት፣ ወ/ሮ መቅደስ፣ አቶ አብርሃም፣ አቶ ደረጀ፣ አቶ ታደለ፣ ዶ/ር ዘለቀ፣ አቶ አሻግሬ)
- 19/02/2005 (ወ/ት ሙሉመቤት፣ ው/ሮ መቅደስ፣ አቶ አብርሃም፣ ዶ/ር ዘለቀ፣ አቶ አሻግሬ፣ አቶ ደረጀ፣ አቶ ታደለ)
- 12/04/2005 (ወ/ት ሙሉመቤት፣ ወ/ሮ መቅደስ፣ አቶ አብርሃም፣ ዶ/ር ዘለቀ፣ አቶ አሻግሬ፣ አቶ ደጀኔ )
.
በመጀመሪያው ስብሰባ ላይ ከሥራ አስኪያጅ ኮሚቴ ውስጥ በቁጥር አራት የሚሆኑትና ከተጋበዙት እንግዶች መካከል ደግሞ በቁጥር ሶስት የሚሆኑት ተገኙ። የተገኙት እንግዶች በቁጥር ያነሱ ቢሆኑም የበሰለ አስተሳሰባቸውና ምክራቸው ለሥራችን ጠቃሚና መሰረት ጣይ ሆኖ አግኝተነዋል፡፡ በአጠቃላይ ሥራችንን እንድንቀጥልበት የሚያደርገው ዋናው ምክንያት የነዚህ ጥቂት ሰዎች በተደረጉት ሦስት ስብሰባዎች ላይ በመገኘት ሊሆንልን ችሏል፡፡ ከሃሳብ መስጠትም አልፎ አይዟችሁ፣ በርቱ እያሉ ድጋፋቸውን፣ ምክራቸውን፣ ጊዜያቸውን፣ ስለለገሱን እጅግ በጣም የሚመሰገኑ ናቸው፡፡ "ወደፊትም አስፈላጊ በሆነ ጊዜ የሚችሉትን ከማድረግ ወደኋላ አንልም" በማለት ቃላቸውን ሰጥተውናል፡፡
.
በስብሰባው የተገኙት እንግዶቻችን ካቀረቧቸው ሃሳቦችና አስተያየቶች ውስጥ ...
* በሥራ አስኪያጅ ኮሚቴ ውስጥ ሆነው ማህበሩን የሚያንቀሳቅሱት ግለሰቦች ጊዚያቸውን መስዋዕት በማድረግ ለማህበሩ ለሚያደርጉት ትልቅ ሥራና ተሳትፎ ሊመሰገኑ ይገባል፡፡ ዓላማዎቹን ከሞላ ጎደል ለማሟላት ይሆናል በሚሉት መንገድ ስራውን ሲያካሂዱ ቆይተዋል:: እንግዲህ መልካም የሰሩት ሁሉ መመስገን ይገባቸዋል:: ማንም ሰው እንዲረዳው የሚፈልገው የማህበሩን መደራጀት በመሆኑና ይህም ከአባላቱ ሃሳብና ምኞት ጋር ግንኙነት ያለው ነው፡፡ ማንኛውም ነገር ሂደቱ የሚሳካው ከጅምሩ ጥሩ ሲሆን ነው፡፡ በመሆኑም ለአንድ ማህበር ህልውና የአመራር ሚና ወሳኝነት የሚያጠያይቅ አይደለምና ተባብሮ ለመስራት እንድያመች አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ውስጣዊ የሆነ ያደረጃጀት ለውጥ በማድረግ የኮሚቴው ይስራ ቅንጅት እንዲሻሻል ማድረግ ይቻላል፡፡ በሥራ አስኪያጅነት ብዙ ጊዜ መቆየት ደግሞ መዘናጋቶችን ሊፈጥር ይችላል። ከዚህም በላይ በማሀበሩ ውስጥ የስራ አስኪያጅ ለውጥ ማድረግ ማለት ማህበሩ በእንቅስቃሴው እየተዳከመ የመምጣቱን ሁኔታ አባላት ስለተገነዘቡት ያው እንዲነቃቃና እንዲንቀሳቀስ ለውጥ ለማድረግ ሊሆን ይችላል:: ሀላፊነትንም ይዞ ብዙ መቆየት ማህበሩን የግል ንብረት ስለሚያስመስለው ለሌሎች በበጎ ፈቃደኝነት መልቀቅና ሌሎች ደግሞ በአዲስ መንፈስ ስራውን እንዲያካሂዱት ማድረግ ይኖርበታል:: ይህንንም ማድረግ "ማህበሩ የከሌና የከሌ ነው እኮ!" የሚባል ጉዳዮች እንዳይፈጠር ይረዳል፡፡
* የዚህ ኮሚቴ ስራ አስኪያጅ ሆኖ መመረጥ ማለት ለኢትዮጵያዊያን ማህበር በነፃ ለመስራት ሃላፊነት መውሰድ ማለት ነው፡፡
* አንድ የኮሚቴ አባል ሲመረጥ መጀመሪያ ፍላጎቱ ቀጥሎም ማህበሩን በነፃ ለማገልገል ሃላፊነት መውሰዱ ሲረጋገጥ ቢሆን ይጠቅማል፡፡
* አመራረጡ ግልፅና ዲዎክራሲያዊ ይሁን፡፡
* አንድ መሪ ያለፈቃዱ መመረጥ የለበትም፡፡
* ፍላጎት ያለው ሰው ቢመረጥ ጥሩ ነው፡፡ ችሎታ ከፍላጎትና ከሃላፊነት መውሰድ በኋላ የሚመጣ ነገር ነው፡፡ ሃላፊነት የሚሰማው ሰው በቅን ልቦና ጠለቅ ብሎ ካሰበ ነገሮችን ይፈጥራል፤ አዲስ ችሎታም ያዳብራል፡፡
* የኮሚቴው ቁጥር መብዛት ሳይሆን ጥራት ላይ ቢያተኩር፡፡ ስለዚህም ቁጥሩን መቀነስ ...
* ተሳታፊ ያልሆኑትን መሪዎች መቀየርና መተካት፡፡
* ተገቢ የሆነውን ሰው አመራር ላይ ማስቀመጥ፡፡
* በአመራር ኮሚቴ ውስጥ የአዲስ መጪዎችና የሴቶች ተሳትፎ እንዲኖር ማድረግ፡፡
* ሴቶች አመራር አባላት ውስጥ ቢጨመሩ ማህበሩ የበለጠ ሊጠነክር ይችላል፡፡
መሪዎቹ እርስ በርሳቸው ቢተባበሩ የበለጠ ውጤት ያመጣሉ፡፡
* አዳዲስ ዜጋዎች በተሳትፎ እንዲያገለግሉ የመምረጥ ሁኔታ ትልቅ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል፡፡
ከዚህም ሌላ ደግሞ በሁለተኛውና በሦስተኛው የስብሰባ ቀኖች እንዲሁ ተገናኝተን ወደፊት ትኩረት ሊሰጣቸው በሚገቡ ነጥቦች ላይ በመወያየት የሚከተሉትን በአጭሩ ከዚህ በታች ቀርበዋል፡፡
.
1- የኮሚቴው ይስራ ቅንጅት እንዲሻሻል፡፡ የስራ ቅንጅት ስንል የማህበሩ ኮሚቴዎች የውስጥ ስራ ክፍፍልና እያንዳንዱም የኮሚቴ አባል የስራውን ድርሻ ሃላፊነት መውሰድና መወጣት ማለታችን ነው፡፡
2- የማህበሩን ሂደት በየተወሰኑ ጊዜዎች ለኢትዮጵያዊያን ማሳወቅ በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ ምክንያቱም አብዛኛዎቹ ኢትዮጵያዊያን ስለ ማህበሩ ሂደት ያላቸው ዕውቀት ዝቅተኛ ሆኖ ስለሚገኝ ነው፡፡
3- ማህበሩ በአሁኑ ጊዜ ከIstituzione, ከRegione, Comune, Provincia etc... ወዘተ ያለውን raporto በመገምገምና በማስተካከል ወቅታዊ ሂደቱን ከቆመበት ቦታ እንዲጀምር .... ..... ...
4- በግለሰብ ደረጃ የተለያዩ እንቅስቃሴና iniziative ሊያደርጉ የሚሹትንና የሚያደርጉትን መንከባከብ (ቋንቋን የሚያስተምሩ፣ ዝግጅቶችን የሚያቀርቡ፣ ባህላችንን አጉልቶ ለሚያሳዩ፣ በተለያዩ ችሎታቸውና ሙያቸው፣ በፈጠራዎች፣ በጉልበታቸውና በሞራላቸው ለመሳተፍ የሚፈልጉትን ወዘተ... ) ትብብርና ድጋፍ እንዲያገኙ ማድረግ
5- ማሕበሩ ውስጥ ተመዝግበው ያለባቸውን ግዴታ ለሚወጡት በሙሉ ሙሉ መብታቸው እንዲጠበቅና በአስፈለጋቸው ጊዜ በማህበሩ መመሪያ መሠረት ትክክለኛው አገልግሎት እንዲኖራቸው ማድረግ፡፡
6- አባል መሆንና አለመሆን ልዩነቱን(ግዴታውን፣ መብቱን፣ ጥቅሙ ንና ጉዳቱን፣ ወዘተ ...) ማስረዳት፡፡
7- የማህበሩን የውስጥ መመሪያ ደንብና ሕግ (STATUTO) አባላት የሆኑት ሁሉ እንዲረዱት ማድረግ። የውስጡን ደንብና ዓላማ በአለማወቅ "ማሕበሩ ለእኔ እንዲህ አላደረገልኝም" የሚባለው እንዳይመጣና ያለመግባባት እንዳይፈጠር በደንብ እንዲረዱት ማድረግ፡፡ ለዚህም ነው አሳጥሮ ወደ አማርኛ መተርጎም ያስፈለገው፡፡ በእርግጥ ዋናው መመሪያና ደንብ የተወሰኑ ገጾች ያለውና በጣሊያንኛ መሆን ይገባዋል፡፡ ነገርግን ለአባላት እንዲስጥ የሚደረገውን በአጭሩ በአንድ ገጽ ላይ ጨምቆ በአማርኛ መተርጎም፡፡ መተርጎሙ እና አሳጥሮ ማቅረቡ የማሕበሩን ዓላማ በቀላሉ ለመረዳት ያስችላል፡፡
8- አባላት በማሕበሩ ያላቸው እምነት የበለጠ እንዲሆን ሂሳብ ነክ ነገሮችንና አስፈላጊ ወይም ጠቃሚ የሆኑ መረጃዎችን በየጊዜው በማቅረብ ማሳወቅ፡፡
9- ለማህበሩ ከኪሳቸው የሚያውጡትና የሚሠሩትን ሰዎች (ቤንዚን፣ ስልክ፣ ጊዜ መስዋዕት ማድረግ፣ ወዘተ ...) ትክክለኛ የሆነ ድጓም እንኳን ባይደረግ ነገር ግን አገልግሎት ስለሚያደርጉ ብቻ ከምስጋና ሌላ ከአንዳንድ የማህበሩ መዋጮ ነጻ እንዲሆኑ ማድረግና ግዴታቸውን እንደሚወጡት የማህበሩ አባላት እኩል የሆነ መብትና ሙሉ አገልግሎት እንዲኖራቸው፡፡
10- በወቅቱ የሚነሱና ወሳኝ የሆኑ ጥያቄዎችን መከታተልና ሌሎችን በማስረዳትም ሆነ ከእነሱም በመረዳት መማማር ይቻላል፡፡
ለምሳሌ
* ለችግረኛ ስደተኞች አገልግሎት እንዲያገኙ informazione እና ልችግራቸው መፍትሔ እንዲያገኙ የሚረዳ ንዑስ ኮሚቴ፣
* የበጎ አድራጊዎች እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ፣ sindacal የሆኑ አገልግሎትና መብት ... ፣ የጤና፣ የሕግ፣ ... አገልግሎት informazione እና ፣ የሽምግልና ኮሚቴ (መቀያየምና መጣላት ሲደርስ ይቅር ለማባባል፣ ለማስታረቅ) ወዘተ ...
* ማህበሩ ፕሮግራሞቹን ሁሉ በተግባር ቢያሳይ አዲስ አባላትን ሊስብ ይችላል፡፡
* ስለማህበሩ ጥቅምና እንቅስቃሴ በማብራራት አባል በመሆን ያላቸውን መብታቸውንና ግዴታቸውን ማሳወቅ፡፡
* ማህበሩ በብዙኃን ዘንድ እንዲታወቅ ቅስቀሳና ማብራሪያ ያስፈልጋል፡፡ ለምሳሌ የሰማው ላልሰማ እንዲነግር በማድረግ፣ ወረቀት በመበተን፣ የተለያዩ comunicazione በመጠቀም ፡- ደብዳቤ፣ ስልክ፣ እሜል፣ መረበ-ገፅ (internet) ...
* አሁንም ከቦሎኛ ውጪ ለሚገኙ አባላት ያለውንና የሚደረገውን እንዲያውቁና እንዲገነዘቡ ለማድረግ በተወካዮቻቸው አማካይነት ግኑኝነትን ማድረግ፡፡ ተወካዮች በሌሉበት ቦታዎች ሁሉ በቁጥር ሁለት እንዲኖር ማድረግ፡፡
* የስብሰባ ቀጠሮ ሲደረግ አብዛኛዎቹ (ከግማሽ በላይ) በሚፈልጉበት ቀንና ሰዓት እንዲሆን መሆን አለበት።- ኮሚቴው በአዲስ መንፈስ ተቻችሎ ለመስራትና ከነበረው ኮሚቴው ጥፋቶች ከአሉ አርሞ ለማለፍ መሆኑን አጥብቀን እንገልጻለን። በአዲስ መንፈስ ለማካሄድ የሚያደርገው ጥረት እንቅፋት እንዳይገጥመው
* በድምፅ ብልጫ የሚወሰኑ ጉዳዮች ላይም ብዙ እንዳይንዛዛ ፍሬ ነገሩን ወስዶ ችግሩ እንዲቃለል ማድረግ
* አዲሱ ኮሚቴ በመንቀሳቀስ ማህበሩን ሕጋዊና ህልውና እንዳለው ሆኖ መቀጠል አለበት፡፡
* በስደት ጥያቄ ችግር ለገጠማቸው ወገኖች ማህበሩ መፍትሔ እንኳን ባያገኝ ችግሮቻቸው እንዲቃለል ማህበራዊ ትግሎች ላይ በመሳተፍና ድምጽን በማሰማት እንዲቃለል ጥረት እንዲያደርግ (እስከዛሬ ግን ይህ ሁኔታ አልነበረም::)
* አባሎቹም በተወሰኑ ጊዜያት ሊታደሱ የሚችሉ ፎቶ ያለበት የመታውቂያ ደብተር ይኖራቸዋል::
* ከአሁን በፊት ያልተደረጉና አዳዲስ አሠራሮች ይጠቅማሉ ከተባለ እንዲፈጸም መሆን አለበት::
* የፈረንጆችም ሆነ የእኛ ዓመት በዓላት (የክርስቲያንም ሆነ የእስልምና ኃይማኖት) ሲያከብሩ የመልካም ምኞትን ይገልፃል:: እነዚህንም በዓላቶች ጊዜውና ቦታው ከፈቀደለት በሚመቸው ሁኔታ ሊያከብር ይችላል፡፡
* የኮሚቴው ሕጋዊ አካልነት እስከሚቀጥለው ምርጫ ጊዜ በአመራር ይቆያል:: የአመራር አባላት ምርጫ የሚካሄደውም በዋናው የአባላት አጠቃላይ ስብሰባ ተጠርቶ በአባሎች መራጭነትና ተመራጭነት ይሆናል::
* ሌላው ደግሞ የማህበርን ዓላማ ለግል፣ ለቡድን፣ ለድርጅት ለጥቅም ለማዋል በሚደረግ የግለሰቦች ጥረት መካከል ስህተት እንዳይሠራና እንዳይፈጠር፣ የማህበሩን ስም ማንም እንዳይጠቀምበት ማድረግ የሁሉም አባላት ግዴታ ነው:: የግል ጥቅምን በማህበር አሳቦ ለማራመድ እስካልተፈለገ ድረስ የሚሰራ ሁሉ ሊሳሳት ይችላል:: እንዚህንም ስህተቶች በየጊዜውና ወዲያው በማረም ወደፊት ይቀጥላል፡፡
* ማህበሩ የፖለቲካ ድርጅት አገልጋይ ነው እንዳይባልና አባላትም ጥርጣሬ እንዳያድርባቸው በቅርቡ ሆነው የሚከታተሉት ታዛቢዎቹ የራሱ አባላት ናቸው፡፡ ከማንም የፖለቲካ ፓርቲ መዳፍ አይንተራስም:: ከፖለቲካ ነፃ መሆን ማለትም ከፓርቲዎችና ከመንግስት ተፅእኖ የሚያገልለው መሆኑ ነው:: ከፖለቲካው ብቻ ሳይሆን ከዘርና ከኃይማኖትም እንቅስቃሴ ነፃ መሆኑን እያረጋገጠ ይሠራል::
* ጥሩዎቹ ነገሮች ባንዲት ነገር ጉድለት ምክንያት መፍረስ የለባቸውም፡፡
* ከእህት ማህበራት ጋር መነጋገርና ሃሳብ መቀያየር ይጠቅማል፡፡
* ለወደፊት ጥናት በማድረግ የሰውን ፍላጎት ለማወቅ መሞከር ጥሩ ነው፡፡
.
ማህበር ማለት ማንኛውም አይነት የጋራ ግብ የሰበሰባቸው አባሎች ውዴታዊ የኅብረት ህላዌ ነው። አላማውም አካሉ ለሆኑት አባሎቹ ጥቅም ባለማቋረጥ መሥራት ነው። የማህበርተኞቹን ግብና መሠረታዊ ጥቅሙ ዓላማ ግብሩ እንድሆን ያደርጋል። ማህበሩም ይኖር ዘንድ አባላቱ ለሕብረቱ የሚለግሱት አስተዋጽኦ መኖር አለበት። አባላት ምንም አይነት አስተዋጽኦ የማያደርጉ ከሆነና ወይም ማህበሩ የሚያስተባብርበት ምክንያት ከሌለው መንምኖ ይቀራል።

Nessun commento: