ፖሞዶሮና ፓስታ ቅርጭም አደርግና
አንድ ጣሳ ቢራ ጭልጥ አደርግና
ተመስገን እላለሁ ኑሮ ይባልና።
አንድ ጣሳ ቢራ ጭልጥ አደርግና
ተመስገን እላለሁ ኑሮ ይባልና።
.
ስፐር ማርኬት ቡስጣ ስሸከም እውልና
ስህን ሬስቶራንት ሳጥብ አመሽና
በኩራት እተኛለሁ ነገም ሌላ አለና።
ስፐር ማርኬት ቡስጣ ስሸከም እውልና
ስህን ሬስቶራንት ሳጥብ አመሽና
በኩራት እተኛለሁ ነገም ሌላ አለና።
.
ከቀናኝ ፊሶ ሥራ አገኝና
ወይም ሽማግሌ ጠባቂ እሆንና
ትላንትን እደግማለሁ ዛሬም እንደገና።
ከቀናኝ ፊሶ ሥራ አገኝና
ወይም ሽማግሌ ጠባቂ እሆንና
ትላንትን እደግማለሁ ዛሬም እንደገና።
.
ጊዜው ሲገሰግስ ዘመኑም ሲረዝም
ሥራዬን ለዘመድ ለወዳጅ አልነግርም
እርዳኝ ባይ ጠያቂ በጭራሽ አልወድም
አገር ግባ የሚለኝ ምክርም አልፈቅድም።
ጊዜው ሲገሰግስ ዘመኑም ሲረዝም
ሥራዬን ለዘመድ ለወዳጅ አልነግርም
እርዳኝ ባይ ጠያቂ በጭራሽ አልወድም
አገር ግባ የሚለኝ ምክርም አልፈቅድም።
.
ባገር ያለ ሁሉ ከንቱ ይመስለኛል
የፈረንጁ ነገር ክሱም ይደንቀኛል።
ባገር ያለ ሁሉ ከንቱ ይመስለኛል
የፈረንጁ ነገር ክሱም ይደንቀኛል።
.
እንደመልካም ነገር ተሰደድኩ እላለሁ
ግን ክብር ያለሀገር እንደሌለ አውቃለሁ።
እንደመልካም ነገር ተሰደድኩ እላለሁ
ግን ክብር ያለሀገር እንደሌለ አውቃለሁ።
.
ዛሬ አያችሁ እንጂ ሳድር በሰው ሀገር
ከዋሉ ካደሩ ለእኔም አለኝ ምድር።
ዛሬ አያችሁ እንጂ ሳድር በሰው ሀገር
ከዋሉ ካደሩ ለእኔም አለኝ ምድር።
.
ሰው ያለሀገሩ ቢበላ መቅመቆ
መከበር አለበት ሰውነቱ ታውቆ።
ሰው ያለሀገሩ ቢበላ መቅመቆ
መከበር አለበት ሰውነቱ ታውቆ።
.
ሰው ክለሀግሩማ ካለቦታው
ብሳና ይሆናል ሸንኮራ አገዳው
መህይም ይመስላል ብዙ እውቀት ያለው።
ሰው ክለሀግሩማ ካለቦታው
ብሳና ይሆናል ሸንኮራ አገዳው
መህይም ይመስላል ብዙ እውቀት ያለው።
.
ካገሩ የወጣ ሀገሩ እስኪመለስ
ኑሮውን ይገፋል ክብሩን በማስገሰስ።
ካገሩ የወጣ ሀገሩ እስኪመለስ
ኑሮውን ይገፋል ክብሩን በማስገሰስ።
Nessun commento:
Posta un commento