venerdì

በጣሊያን የውጪ ዜጎችን ይሚመለከት ወቅታዊ ሁኔታ


di Abraham Zewdie
ኢጣሊያ - የውጭ ዜጎች የፍልሰት መመሪያ በአዲሱ የፕሮዲ አስተዳደር እየተለወጠ እንደሚገኝ የሰሞኑ የዜና መረጃዎች ያወሳሉ። አዲሱ መንግስት የBossi-Fini የፍልሰት መመሪያ ጽንሰ ሀሳቦች እንደሚቀየሩና እስካሁንም የተቀየሩትን ሰሞኑን በምክር ቤት እንዲፀድቅ ያቀርባሉ።
ከዚህ በታች ትኩረት ከተሰጠባቸው፣ በውሳኔ ከአሳለፏቸው መካከልና ከተነጋገሩባቸው የመመሪያው ፅንሰ ሃሳቦች በንዑስ አርዕስት ሰፍረዋል።...
.
ስለ ካርታ ዲ ሶጆርኖ (Carta di Soggiorno)
በጣሊያን ኑሮአቸውን 5 ዓመት ያደረጉ የውጪ ዜጎች ካርታ ዲ ሶጆርኖ ሊያግኙ እንደሚችሉ ተገለጸ። እንደ Bossi-Fini የውጭ ዜጎች ፍልሰት መመሪያ "ካርታ ዲ ሶጆርኖ ለማግኘት የ6 ዓመት የመኖሪያ ፍቃድ ያላቸው መሆን አለባቸው" ይላል። አሁን ያለው የአዲሱ መንግሥት አስተዳደር ደግሞ መመሪያውን በማሻሻል እና አንድ ዓመት በመቀነስ ኑሮውን 5 ዓመት ያደረገ ከሆነ ሊሰጠው እንደሚችል" ነው። ይኼም በብሔራዊው የህዝብ ምክር ቤት (parlamento) ድምጽ ተሰጥቶበት ከአሸነፈ በሚኒስትሮች ምክር ቤት የህጉን ረቂቅ አንቀጾች ቀምረው በአዋጅ እንዲድነገግ ይደረጋል። ከአዋጁም በኋላ ቁጥራቸው ወደ በመቶ ሺዎች የሚደርሱ የውጪ ዜጎች ሊገለገሉበት እንደሚችሉ ተገምቷል። ከሚፀናበት ጊዜ ጀምሮ ምዝገባዎችንና ማመልከቻዎችን በማስገባት የዕድሉ ተጠቃሚ መሆኑ ይበጃል የሚሉ የውጪ ዘጎች ብዙኃን ናቸው።
የአውሮፓ ሕብረት የጋራ የሆነውን የፍልሰት መመሪያ (2003/109/CE) እንዳወጣ ብዙ ሳይቆዩ አንዳንድ አባላት ሀገሮች በአዋጅ እንዲፀና በማድረግ እየተጠቀሙበት ይገኛሉ። ይህ ደግሞ በጣሊያን ዘግይቶ ቢደረግም በዚሁ የአዲሱ የመንግስት አስተዳደሯ ውስጥ በተግባር ላይ እንዲውል አሁን ጥረት እየተደረገ ነው ማለት ይቻላል።
ይህንን ካርታ ዲ ሶጆርኖ መያዙ ለምን ይጠቅማል? ለሚለው ጥያቄ የጣሊያን ሀገር አስትዳደር ሚኒስትር የሆኑት ጁሊያኖ አማቶ ሲመልሱ "ጣሊያን ሀገር ያሉትን የውጭ ተወላጆች የስደተኝነት ኑሮ በመጠኑም ቢሆን ሊያሻሽል ይችላል" ነው የሚሉት። ቀጥለውም "አንድ የውጪ ሀገር ዜጋ 5 ዓመት ተቀምጦ እዚሁ ጣሊያን ሀገር ከሚኖሩ የአውሮፓ ሕብረት አባላት ዜጋዎች የማያንስ መብት እንዲኖራቸው ይገባል። ምንም ልዩነት ሳይደረግ በሰላም ሰርቶ ለመኖር እንዲችሉ፣ ትምህርት ተምረው የወደፊት የኑሮ እቅዳቸውን ለማውጣት እንዲችሉ መንገዱን ማስተካከል ይገባናል። ወደፊትም ከዚህ ጋር ተያይዞ መመሪያው ውስጥ ያሉትን ነጥቦች በማሻሻል የረጅም ጊዜ ኑሮ ለሚያደርጉት መብታቸው ከሀገሯ ዜጎች እኩል እንዲሆንላቸው መደረግ አለበት" በማለት አሳስበዋል።
.
ቤተስብን ለማስመጣት ... (Ricongiungimento)
አንድ የውጪ ዜጋ መኖሪያውን ለረጅም ጊዜ ጣሊያን ሀገር አድርጎ የቅርብ ቤተሰቡን አስመጥቶ ተቀማጭነቱ እዚሁ እንዲሆን ለማድረግና ለማስፈጸም የሚወስደው ረጅም ጊዜ ነው። ውጣ ውረድ የሚበዛበት ስለሆነ ይህን ውስብስብ ስርዓት አስተካክሎ በአጭር ጊዜ እንዲፈፀም የሚቻልበት ሁኔታ መፈጠር አለበት።
የሀገር አስተዳደር ሚኒስትር ጁሊያኖ አማቶ በምክር ቤት ውስጥ እንደገለጹት "ይህንን ሁኔታ የሚመለከቱ ጉዳዮችን ለማቃለል የአውሮፓ ሕብረት ያወጣውን መርሆችን መከተል እንደሚቻል" ተናግረዋል። ሚኒስትሩም በመቀጠል "ከረሃብ የተረፉትን ልጁ ወይም ወላጁን ለማስተናገድ በመኖሪያ ቤቱ ሜትር ስፋት መወሰኑ ብዙ ትኩረት የሚሰጠው መሆን የለበትም። ለደህንነታቸውና የጤና ችግር የማያመጣ ወይም የሚፈቀደውን ክራይቴሪያ ከአሟላ ይበቃል" ነው ያሉት። እንደገናም በማከል "የቤተሰብ ፍቅርን ማግኘትና መቀራረብ ለሁሉም ዜጋዎች ስበዓዊ መብታቸው መሆኑን መዘንጋት የለበትም" ብለው ደምድመዋል።

እየፈለሰ ለሚገባው የስደተኛውን ቁጥር ለመወሰን ...
ሀገር አስተዳዳሪው ሲያብራሩ "በአሁኑ ጊዜ ዋናውና ወቅታዊው ጥያቄ እየፈለሰ ለሚገባው ስደተኛ ቁጥሩን በየዓመቱ ምን ያህል እንደሆነ መወስን ሳይሆን ለጣሊያን የኢኮኖሚ እድገት አስተዋጽኦ እስከአለው ድረስ እና የሕብረተሰብ ስርዓት እስካልተጓደለ ድረስ "እንኳን ደህና መጡ" ብሎ መቀበል እንጂ! ምን ችግር አለ? እስከሚቻለን ድረስ በመቀበልና ስርዓትን በማሲያዝ መወጣት እንችላለን" ነው ያሉት። ለጋዜጠኞች ቃለ ጥያቄ ሲመልሱም "የዓለም አቀፍን የሰበዓዊነት መብቶቹን እንዲከበር ለማድረግ በሚቻለን መንገድ ከመጣር ወደኋላ ማለት አይገባንም" ብለዋል። ...

በ nulla osta ሥራ መቅጠር ...
ሌላው ደግሞ በ Bossi-Fini የፍልሰት መመሪያ መሰረት የአውሮፓ ሕብረት አባላት የሆኑት የውጪ ዜጋዎችን አሠሪው በnulla osta አማካይነት ሥራ የማግኘቱ ዕድላቸው በጣም የሰፋ እንደነበረና አሁን ግን ይኼንን nulla osta እንዲቀር ተደርጎ ነፃና እኩል የሆነ የሥራ አቀጣጠር ላማንኛውም ዜጋ እንዲኖር ይደረጋል። ...

የጥቁር ሥራን ለማስወገድ ... (Lavoro nero)
በየፋብሪካውና በቤተሰብ አገልግሎት ውስጥ ብቻ የጥቁር ሥራ እየሠሩ ያሉት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ስለሆኑ ሁሉም regolarizzare መደረግ አለባቸው። ኢጣሊያዊው የአውሮፓው ሕብረት ምክትል ሊቀመንበር ማርኮ ፍራቲኒ አያይዘው "በ2004 ዓም በአንድ የእስታቲስቲክ ጥናት ላይ በሌሎች የአውሮፓ ሕብረት ሀገሮች ውስጥ በጥቁር ሥራ ላይ ተሰማርተው የሚገኙት ከ4% - 5% ያህል ነው። ነገርግን በኢጣሊያ ቁጥራቸው በጣም ከፍ ብሎ እንደሚገኝና እስከ16% - 17% የሚደርስ ነው" ብለዋል። እሳቸውም በመቀጠል "ይህንን በጊዘው ስራዓት ማሲያዝ ያስፈልጋል። ለዚህም በየክፍለሀገሩ የሚገኙት የጣሊያን ማዕከላዊ አስተዳደር ክፍሎች በጥቁር ሥራ ላይ የተሰማሩትን የውጪ ዜጋዎች ሙሉ በሙሉ በ regolare ሥራ እንዲሰማሩ ለማስቻል ሁሉም ተሳትፎ ማድረግና ይሚቻለቸውን ግዴታ እንዲወጡት ብዙ ይጠበቅባቸዋል" ብለዋል።
.
የጣሊያን ዜግነት በ5 ዓመት ...
...........................................................
...........................................................
...........................................................
...........................................................
በጣሊያን ከ5 ዓመት በላይ የተቀመጡ ምን ያህል የውጪ ዜጎች አሉ?
የ Caritas /Migrantes የስታቲስቲክ መዝገብ እንድሚያስረዳው "በጣሊያን ኑሮአቸውን 5 ዓመት ያደረጉ የውጪ ዜጎች ቁጥር ወደ 900 ሺ ይደርሳሉ። ከ2 ዓመት በኋላ ደግሞ በ2002 ዓም regolarizzati የሆኑት 650 ሺ ዜጎች ተጨምረው በጠቅላላው 1 ሚሊዮን ተኩል የሚሆኑት ዜግነቱን የመውሰድ መብት ይኖራቸዋል። ታዲያ አልበዛም? እንዴት ሊሆን ነው? ለሚለው ጥያቄ የሀገር አስተዳደር ሚኒስትር ጁሊያኖ አማቶ ሲመልሱ "እዚህ ላይ ቁጥርን በሚመለከቱ ነገሮች መጠንቀቅ ያለብን ይመስለኛል። ዜግነት ለመያዝ በየዓመቱ ቁጥራቸው እስከ 18 ሺህ ያህል የሚሆኑት የውጪ ዜጎች ሊቀርቡ ይችላሉ የሚል ግምት ነው ያለን። እንደውም በዚህ የቁጥር ገደብ ውስጥ ዜግነት ለማግኘት ማመልከቻ ያቀረቡት ብቻ ሳይሆን እዚህ ያሏቸውን ልጆቻቸውንም ይጨምራል። ምክንያቱም በጣሊያን በየዓመቱ ከውጪ ዜጎች የሚወለዱት ህፃናት ብቻ ወደ 50 ሺ ይጠጋሉ። ከእነዚህም ውስጥ ዜግነቱን የሚያገኙት ሁሉም አይደሉም። ወላጆቻቸው ኑሮአቸውን በጣሊያን ከ5 ዓመት በላይ ላደረጉት ብቻ ነው። ከእነዚህም ውስጥ በየዓመቱ ዜግነቱ ሊሰጣቸው ከሚችለው የቁጥር ገደብ ውስጥ በማስገባት ነው" ብለዋል። ....
ጠቅላይ ሚኒስትር ሮማኖ ፕሮዲ በማከል "10 ዓመት መሆኑ ቀርቶ 5 ዓመት መደረጉም ብዙዎቹ የአውሮፓ ሀገሮች የሚከተሉት በመሆኑ አንድ አይነት መስመር ለማሲያዝ ነው። በእንደዚህ አይነት ጉዳይ ጣሊያን ከሌሎቹ የአውሮፓ የጋራ መርሕ ወደኋላ ስለምትገኝ ነው" ብለዋል፡ ጨምረው ሲያስረዱ "መጠን በማድረግ፣ ሌሎች መመዘኛዎች በማስገባትና እንዲሁም አመልካቾቹን በማወዳደር ገደብ እንዲኖረው ማድረግ ይቻላል።
ለምሳሌ
1- ከዚህ በፊት ዜግነቱን ለማግኘት ብቻ ሲባል የውሸት ጋብቻ የሚፈፅሙት ላይ ጥንቃቄ ይደረጋል።
2- የቋንቋ ችሎታቸውን በመመዘን...
3- ..............." ብለው የቃለ መጠየቁን መደምደሚያ ሰጡ።
.
ሌሎች በስብሰባው ላይ ከተሰጡት አስተያየቶች ውስጥ (አስፈላጊ ከሆነ በዝርዝር ትንታኔዎችን ወደፊት እናቀርባለን)
ይህ በጣሊያን የረጅም ጊዜ የመኖሪያ ፈቃድ ማግኘት የሚቻልበት ሁኔታ በጊዜው ከተቃለለ ወደፊትም ከዚሁ ጋር የተያያዙ ሁኔታዎችን እንዲስተካከል በማድረግና ስርዓት በማስያዝ የተወሰኑ የውጪ ዜጎች ችግር ለማቃላል ይረዳል።
ከእነዚህም ውስጥ አንዳንዱን ንጥብ
ለምሳሌ ...
* ዜግነትን በሚመለከት ከተሻሻሉት አንዳንድ የህጉ ረቂቆች ውስጥ ከዚህ በፊት በጋብቻ ምክንያት ዜግነቱን የሚያገኘው ማመልከቻውን ከአቀረበበት ጊዜ አንስቶ 2 ዓመት ያስፈልገው ነበር። አሁን በግማሽ ዓመት (6 ወር) ሊያገኝ ይችላል።
* በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚገኙትም የተሻለ አማራጭ ዕድልና እኩል መብት እንዲኖራቸው፣
* በሌሎች የአውሮፓ ማህበር አባላት ሀገሮች ውስጥ ያለምንም እንቅፋት መዘዋወርና ሥራ የመሥራት ፍቃድ ለማግኘት የሚችሉበትን መብት ማስያዝ፣
* ለተገን ጥያቂዎች ዓለምአቀፋዊ የፖለቲካ ጥገኝነት መብት እንዳይነፈጋቸው ጥረት ማድረግ፣
* በጣሊያን ከረጅም ጊዜ የኑሮ ሁኔታ ጋር በተያያዘ የፖለቲካ ምርጫ ላይ ተስትፎ እንዲኖራቸው ማድረግ፣
* ወደፊት የ5 ዓመት መኖሪያ ፈቃድ ያለው (ካርታ ዲ ሶጆርኖ ብቻ ሳይሆን) የተወሰኑ ... አሟልቶ የተገኘውን ዜግነቱንም መያዝ እንደሚችል ...
* ሥራ ፈላጊ ለሆነው የውጪ ሀገር ዜጋ በሩ እኩል ክፍት እንዲሆንለት፣
* መብታቸውና ስበዓዊ ክብራቸው እንዲጠበቅ፣
* ደህንነታቸው አስተማማኝ እንዲሆን፣
... ይቀጥላል ... ይቀጥላል ... ይቀጥላል ... ይቀጥላል ... ይቀጥላል ... ይቀጥላል ... ይቀጥላል ...

Nessun commento: