giovedì

የጣሊያን ምንስትሮች ምክር ቤት ለ 80.000 ሺህ የዉጭ አገር ዜጎች ጊዜያዊ የስራ ፈቃድ ሕግ አፀደቀ


አ.አ.አ. በ 8/11/2007 የጣሊያን ምንስትሮች ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ ባደረገዉ ስብሰባ ሰማኒያ ሺህ ያህል ለሚሆኑ የዉጭ አገር ዜጎች ጊዜያዊ የስራ ፈቃድ ማግኘት እንዲችሉ አዲስ ሕግ አፀደቀ::
ይህ አዲስ ሕግ ተግባራዊ የሚሆነዉ በነጋሪት ጋዜጣ ላይ ታትሞ ከወጣ በኋላ ስለሆነ ትንሽ ጊዜ መጠበቅ ያስፈልጋል::
የሚመጡትም የዉጭ አገር ዜጎች የስራ ክፍል በእርሻና በቱሪዝም ሲሆን በብዛት የሚመጡትም ከሚከተሉት አገሮች ይሆናል:-
- ሰርቢያ;
- ቦዝኒያ፣
- የቀድሞዉ ይዩጎዝላቪያ ረፑብሊክ ማቸዶኒያ;
- ክሮዋዝያ;
- ህንድ;
- ፓክስታን;
- ባንግላደሽ;
- ስሪላንካ;
- ዩክራይና;
- ቱኒዝያ;
- አልባኒያ;
- ሞሮኮ;
- ሞልዳቪያ;
- ግብፅ ወዘተ ናቸዉ:
በ 2005፣ 2006፣ 2007 የስራ አመት በጊዜያዊ ሰራተኛነት ጣሊያን አገር የመጡ ግለሰቦች ሁሉ ማመልከቻቸዉን ማቅረብ ይችላሉ::
የማመልከቻ ማቅረቢያዉ ሁኔታ ካሁን ቀደም እንደጠቀስኩት በእንተርኔት ይሆናል::

ከዶ/ር ዘለቀ እሬሶ


Nessun commento: