mercoledì

የጣሊያን የምንስትሮች ምክር ቤት 170.000 የዉጭ ሀገር ስራ ፈላጊዎች ጣሊያን አገር መግባት ይችሉ ዘንድ ሰሞኑን አዲስ ህግ አረቀቀ


ከዶ/ር ዘለቀ እሬሶ
14 11 2007

ካሁን በፊት በተለያዩ አጋጣሚዎች እንደገለፅኩት ሁሉ የጣሊያን መንግስት በየአመቱ ምን ያህል የዉጭ ሀገር ዜጎች ሰራተኞች ለሀገሪቱ ለስራ እንደሚያስፈልጉ በመተመን ጣሊያን እንዲገቡ በየጊዜዉ የአመቱን ህግ ይደነግጋል:: በመሆኑም በዚህ በያዝነዉ የአመት በጀት ፕሮግራም መሰረት በአንቀፅ 2 እንደተመለከተዉ የጣሊያን መንግስት 170.000 ለሚሆኑ የዉጭ ሀገር ዜጎች ማለትም የአዉሮፓ ህብረት አባል አገር ዜጎችን ሳይጨምር በስራ ምክንያት ጣሊያን አገር መግባት የሚያስችል አዲስ ህግ አዉጥቶአል::

የህጉንም ይዘት አጠር ባለ መልኩ ለአንባቢያን ለማስቀመጥ ያህል:-
በመጀመሪያ ደረጃ በህጉ አንቀፅ 2 ላይ እንደተጠቀሰዉ ሁሉ ቁጥራቸዉ 47.100 ያህል ሰራተኞች ከተለያዩ አገሮች ማለትም ክጣሊያን ጋር የቅርብ የጋራ ስምምነት ተፈራርመዉ ከነበሩት ከሚከተሉት አገሮች የሚመጡ እንደሆኑ ተጠቅሷል:-
- ከአልባንያ 4.500;
- ከአልጀሪያ 1.000;
- ከባንግላደሽ 3.000;
- ከግብፅ 8.000;
- ከፍሊፒን 5.000;
- ከጋና 1.000;
- ከሞሮኮ 4.500;
- ከሞልዳቪያ 6.500;
- ከናይጄሪያ 1.500;
- ከፓክስታን 1.000;
- ከሴኔጋል 1.000;
- ከሶማሊያ 100;
- ከስሪላንካ 3.500;
- ከቱኒዚያ 4.000;
- ከተቀሩት አገሮች 2.500::

የስራዉስ ምክንያትና መስክ ምን ምን ይሆናል?
- በቤት ሰራተኛነት 65.000;
- በህንፃ ስራ ሰራተኛነት 14.200;
- በከፍተኛ ትምህርት ተመርቀዉ የሙያ ሃላፊ የሆኑ 1.000;
- በሹፌርነት ልዩ የአዉሮፓ ሰርቲፊኬት ያላቸዉ 500;
- በአሳና ባህር ስራ ላይ 200;
- በተቀሩት የስራ መስኮች 30.000;
- ትምህርትን በስራ በመቀየር 3.000;
- በሙያ ኮርስ ስልጠና 1500;
- በትምህርት 2.500;
- እና በመሳሰሉት::

መቼ ማመልከት ይቻላል?
ይህ ህግ በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ በወጣ በአስራ አምስተኛዉ ቀኑ ማመልከት ይቻላል:: ማመልከቻዉን የሚያቀርበዉ ቀጣሪዉ ግለሰብ ፎርሙን እንተርኔት በመጠቀም መሙላት ይኖርበታል::
zeleke_eresso@yahoo.it
Tel. 3395764139

Nessun commento: