lunedì

በፖስታ ቤት የደረሰኝ ወረቀት ነፍስህን አድን



የጣሊያን ቢሮክራሲና ማለቅያ የሌለዉ የዉጭ ሀገር ዜጋዉ ስቃይ
20 07 07
ከዶ/ር ዘለቀ እሬሶ
ሰሞኑን ከተለያዩ ሰዎች “የመኖሪያ ፈቃድ ወረቀቴን ለማሳደስ ፖስታ ቤት ካስገባሁ ሁለት፣ ስድስት፣ ዘጠኝ፣ አስራ ሁለት ወራት ወዘተ ሞላኝ ዳሩ ግን እንዃንስ ወረቀቱ ታድሶ ሊላክልኝ ቀርቶ ፎቶግራፍ እንዳቀርብ እንኳን የጠየቀኝ ሰዉ የለም” በማለት ብሶታቸዉን ሲገልጹ እሰማለሁ:: ከዚሁ የቢሮክራሲ ዉጣ ዉረድ የተነሳ በብዙ የሚቆጠሩ የዉጭ ሀገር ዜጎች ሰራተኞች ቀደም ሲል ከነበራቸዉ የስራ መስክ ሊባረሩ ተዳርገዋል፣ ፈልግዉም ሌላ ስራ ቢያገኙ የመኖሪያ ፈቃድ ወረቀቱ በመዉደቁ የሚቀጥራቸዉ ድርጅት አይኖርም:: ይህ ብቻ ሳይሆን መዘዙ እየበዛ ይመጣና የዉጭ ሀገር ዜጋዉ ስቃይ ይጨምራል፣ መፍትሄዉ የፖስታ ቤት ደረሰኝን በማሳየት በሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚንስቴር የስራ አጦች ሊስት ላይ መመዝገብ መቻል ይሆናል:: የመኖሪያ ፈቃድ ወረቀቱን ለማሳደስ ፖስታ ቤት አስገብቶ የፖስታ ቤት ደረሰኝ ተሰጥቶት በመጠባበቅ ላይ ያለ ግለሰብ ሁሉ በየክፍለ ሀገሩ የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚንስቴር ቢሮ በመቅረብ መመዝገብ እንደሚችል በቁጥር 19/2007 የጣሊያን የሀገር ዉስጥ ሚንስቴር ሰሞኑን ደንግጓል::

Nessun commento: