lunedì

ሶጆርኖ እስከሚሰጡኝ ጊዜ ቢፈጅም የራሱ ጉዳይ


መምሪያ

28 07 2007

ምንም እንኳን ይህ መምሪያ ለዚህ የውጪ ዜጎች ለእረፍት ጉዞዋቸው እንዲጠቀሙበት ዘግየት ብሎ የወጣ ቢሆንም ሰሞኑን በሀገር አስተዳደር ሚኒስትር ጁሊያኖ አማቶ የተፈረመበት መምሪያ በመሆኑና ለሁላችንም መልካም ዜና ስለሆነ መልዕክቱን እንዲያነቡት ስናደርግ ከደስታ ጋር ነው።
"ማንኛውም የውጪ ዜጋ የመኖሪያ ፈቃዱን ለማሳደስ ማመልከቻ ያስገባ ከሆነና ለዚህም ደግሞ የፖስታቤት ደረሰኝ የተሰጠው ከሆነ መብቱ በሙሉ ሙሉ ሶጆርኖ በኪሱ ከያዘው እኩልና የማያንስ ነው" የሚል ነው። ስለዚህም ሥራ መቀየር፣ አዲስ የቤት ኪራይም ሆነ የሥራ ኮንትራት መውሰድ፣ የመኪና መንጂያ ፈቃድ ማውጣት፣ የትውልድ ሀገሩ ደርሶ መመለስ፣ ወዘተ...ወዘተ...ወዘተ...ወዘተ...
በአጠቃላይ የፖሊስ ጽህፈትቤቱ (ኩዌስቱራ) ሶጆርኖ እስከሚታደስላቸው ድረስ በመጠበቅ ላይ ያሉትን የሚነፍጋቸውን መብቶች አሁን ነጻ ያደርጋቸዋል። ሶጆርኖ በኪሱ ካለው ጋር እኩል መብት እንዲኖረው ያደርጋል ማለት ነው።
መምሪያውን ከዚህ ያውርዱ

ማስገንዘቢያዎች
* የትውልድ ሀገሩ ደርሶ መመለስ ለሚፈልግ ለፋሲካ፣ ለገና፣ እንዲሁም ለበጋው እርፍት ብቻ ሳይሆን በማንኛውም ጊዜ ትውልድ ሀገር ደርሶ ለመመለስ ይችላል። ነገር ግን ወደ ከጣሊያን በወጣበት በር ተመልሶ መግባት ይኖርበታል። ምክንያቱም ሲወጣ ፓስፖርቱ ላይ ማሕተም የሚያደረግበት የድንበር ፖሊስ ሲገባም ማሕተም ስለሚያደርግበትና መመለሱ የሚመዘገብበ ስለሆነ ነው። ከዚህም በላይ የፖስታቤቱ ደረሰኝ ወይም ጊዜው የወደቀብት ሶጆርኖ ላይም ቁጥጥር ሊኖር ይችላል።
* ሌላው ደግሞ ይህ የፖስታ ቤት ደረሰኘ ወረቀት እንደመጓጓዣ ሰነድ ቢያገለግልም ጉዞው (መነሻውና መድረሻው) የተወሰነ በመሆኑ ከደርሶ መመለሱ ሌላ ወደ ሌሎች የአውሮፓ ሀገር መጓዝ አይቻልም። በፊትም በነበረው ዓለም አቀፋዊ ድንጋጌ መሠረት የ (area schengen) አካባቢ መዟዟር አይቻልም።

ምንም እንኳን ይህ የተፈረመበት ዋና መመሪያ በሥራ ላይ እንዲውል በየቦታው የተላለፈ ቢሆንም ከፖሊስ ጽህፈት ቤቱ ሌላ በየቢሮዎች ሙሉ በሙሉ መሪያውን እንዲጠቀሙበትና በአስቸኳይ ለዚህ የእረፍት ጊዜ ተጓዦች እንዳይተጓጎሉና በቶሎ እንዲፈጸምላቸው የሁላችንም ምኞት ነው። ከዚህም በላይ ይህ መምሪያ በዚህ ዓመት ያለውን ጊዜያዊ የውጪ ዜጋዎችን ችግርና ይህንን እየተጓተተ ያለውን የሶጆርኖ እድሳት ቢሮክራሲ ለማቀለል ተብሎ የተደረገ ሊሆን ስለሚችል በሂደቱ ላይ ለውጦች ሊኖሩት ይችላሉ:: ስለዚህም ወደፊት ለተሻለ ሁኔታ ተስፋ እናደርጋለን።

አብራሃም ዘ. 28 07 2007



Nessun commento: